የኤርትራ መንግስት በቀይባህር ጉዳይ ከማንም ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥ አሳወቀ የኤርትራ መረጃ ሚኒስቴር ባወጣዉ አጭር መግለጫ በቀይባህር ጉዳይ ከማንም ጋር ለድርድር እንደማይቀመጥ አሳዉቋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስለ ውሀዊ አካሎችና ስለ ባህር በሮች የተባለውንና ተብሏል የተባለው ነገር ቁጥር የለውም ያለዉ ሚኒስቴሩ በዚም ያልተገረመ ታዛቢ የለም ሲል ገልጿል። የኤርትራ መንግስትም እንደሁልጊዜው በእንደዚህ ዓይነቱ ጉዳዮች ላይ ለውይይት እንደማይታደም ማረጋገጡን ዳጉ ጆርናል ከሚኒስቴሩ ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል። ይህ ነገር ይመለከተናል የሚሉ ሁሉም አካላት ጉዳዩን እንዳይነኩት የኤርትራ መንግስት አስጠንቅቋል። በቅርቡ በመንግስት የመገናኛ ብዙኃን በተሰራጨ መልዕክት ጠ/ሚ ዐቢይ የባህር በር ጉዳይን አንስተዉ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ማወያየታቸዉ ይታወሳል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news 13.8K viewsedited 11:03