Get Mystery Box with random crypto!

' ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሦስቱ አባቶች መመለስ ታላቅ ደስታ ተሰምቷታል ' - ቅዱስ ሲኖዶስ ከ | ልብወለድ Ethio_Fiction

" ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሦስቱ አባቶች መመለስ ታላቅ ደስታ ተሰምቷታል " - ቅዱስ ሲኖዶስ

ከቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ውስጥ የተወሰደ ፦

" ... በዛሬው ዕለት የቤተ ክርስቲያን ጸሎቷ፣ ሐዘኗና ጩኸቷ ተሰምቶ ወደ ነበረችበት ልዕልናዋና አንድነቷ ተመልሳለች፡፡ ይህ አንድነቷና ልዕልናዋ እስከ ዓለም ፍጻሜ ተጠብቆ ይኖራል፡፡

በቅርቡ በቤተ ክርስቲያናችን ተከስቶ የነበረው ችግርም በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ተፈትቷል፡፡

... በችግሩ አፈታት ወቅት መንግሥት በተለይም ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ፖለቲካዊ ችግሩን በፖለቲካዊ መንገድ ከመፍታታቸውም ባሻገር የቤተ ክርስቲያን ችግር በቀኖናና በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት እንዲፈታ ታላቁን አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡

ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቀደም ሲል ሁለቱን ሲኖዶስ አንድ በማድረግ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አሁንም የቤተ ክርስቲያን አንድነት ተጠብቆ እንዲኖር ላደረጉት መልካም ተግባር ቤተ ክርስቲያን ከልብ ታመሰግናለች፡፡

... ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሦስቱ አባቶች መመለስ ታላቅ ደስታ ተሰምቷታል፡፡ ካህናት፣ ምእመናን በሀዘናችን ተካፋይ የነበራችሁ በሙሉ የዚህ ደስታ ተካፋዮች በመሆናችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት ቅድስት ቤ ክርስቲያን ደስታዋን ትገልጻለች፡፡ "

share - @ethio_fiction