Get Mystery Box with random crypto!

'..........ግጥም ላንብብላችሁ አለ ?! '  ባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ ተፈቀደለት። ግጥሞቹ | ልብወለድ Ethio_Fiction

"..........ግጥም ላንብብላችሁ አለ ?! "  ባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ ተፈቀደለት።

ግጥሞቹ በየሰው እጅ ነው የሚገኙት ከጻፈ በኋላ የትም ይጥለዋል ።  ለነገሩ የግጥም ሐሣብ ሲመጣለት  ዛር እንዳለበት ያደርገዋል... ያጣድፈዋል። 

"  አስዬ ጨብራሪት መጣች ፣ አስዬ  ጨብራሪት መጣች  ፣  አስዬ ጨብራሪት መጣችብኝ  …  " ብሎ ይቁነጠነጣል ።

አስዬ ጨብራሪት የምታስፅፈው ዛር ናት ። ይህች ዛር ከመጣች አሁኑኑ ነው የምታስብለው ።  በዚህ ጊዜ አጠገቡ ካሉ ሰዎች መካከል (ለምሣሌ ስንዱ)  እስኪርብቶ አንስታ የሚለውን ትገለብጣለች ።  አምስት ……  ስድስት ወይም ሰባት ገጽ ሊሆን ይችላል። 
" በቃሉ ነው የሚያወጣቸው "  ሲባል ሰምቻለው ያልተጻፉ ግጥሞቹን ።  ከተጻፈ በኋላ አይሰርዝም  አይደልዝም  ። 

ከዛ  "አንብቢልኝ "   ይላል ።  ታነባለች   " ሸላይ ናት "  ይላል   በቃ  ።  ከእነዚህ ግጥሞች አንዱን አንብቦልን ሲጨርስ አስተያየት ጠየቀን  ።   እኔም የሚደነቀውን አድንቄ   "  ...ግን ከመጠን በላይ ረዥም ነው "    አልኩት  ። ፈጣን መልስ ሰጠኝ  ።   

"  አንተ የበልግ ካፊያ ከሆንክ እኔ የሐምሌ ወጀብ እንዳልሆን ልትከለክለኝ አይገባም  "  አለኝ።  

ቀደም ሲል አጫጭር ግጥሞች አቅርቤ ስለነበር ነው ።  ግጥሞቼ በበልግ ካፊያ የመሰላቸው ። 

"  ጋሽ ስብሐት እንዴት አየሃት?  "  ጠየቀ።

" አልሰማኋትም .... "   አለው ስብሐት ።

"  አትኩረህ እያየኸኝ አልነበር ? "

"   ..........መጀመሪያ ልሰማህ ጓጉቼ ነበር ።   ቆይቶ ግን የግጥሙ ርዝመት ይሁን የቋንቋው ክብደት አላውቅም እኔና አንተን ለመለያየት ምክንያት ሆነን  ።   እናም አየሰማሁህ ጺምህን ሳይ  ፣   ፊትህን ሳይ በስዕል የማውቀው የራሺያው  ዶስቶቪስኪን  መሰልከኝ  ።  አዬ መመሳሰል ብዬ ስገረም ስገረም  ግጥምህን ጨረስከው አንድ ቀን ትደግምልኛለህ!  "   አለው።

※ እንዳለጌታ ከበደ በ2006  ከጻፈውና ካሳተመው ማዕቀብ  መጽሐፍ የተቀነጨበ  ።


#share -----> @ethio_fiction

#comment ---> @Cr7_reunited