Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Today

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio2today — Ethio Today E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio2today — Ethio Today
የሰርጥ አድራሻ: @ethio2today
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.44K
የሰርጥ መግለጫ

ፈጣን አዳዲስ እና የተረጋገጠ መረጃ በእየለቱ ያግኙ።
YouTube :- https://www.youtube.com/channel/UCM0oGovoseqStaFWh2wIi4g

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-31 09:55:09
ነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም

በፈተና ነጥራ የወጣች ሀገር ኢትዮጵያ!!

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ፈተናዎች ያጋጥሟታል። ኢትዮጵያን ፈተናዎች አላዳከሟትም ይልቁንም ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሆና ወደፊት እንድትቀጥል አበርትቷታል።

ኢትዮጵያ ወርቅ ነች። ወርቅ በእሳት ነጥሮ አምሮና ደምቆ እንደሚወጣው ሁሉ ኢትዮጵያም በፈተናዎች አልፋ ለዘመናት ታፍራና ተከብራ ኖራለች ትኖራለችም።

ኢትዮጵያ ፈታኞቿ የውጭ ጠላቶቿ ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ሀገራችንን ፊት ለፊት ገጥመው ማሸነፍ እንደማይችሉ ከታሪክ መዝገብ የተረዱ በመሆናቸው በባንዳና ተላላኪዎች አማካኝነት ፍላጎታቸውን ማሳካት ይፈልጋሉ።

በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የሚጋለበው አሸባሪው የህወሓት ቡድንም እነሱ ያልተሳካላቸውን ሀገር የማፍረስ ህልምቸውን ተቀብሎ መቃዠት ከጀመረ ሰምበትበት ብሏል ብቻ ሳይሆን ከርሟል።

ኢትዮጵያን ፊት ለፊት ገጥመው የሆኑትን እና የሚሆኑትን የሚያውቁት የውጭ ጠላቶቻችን የወስጥ አንድነታችን ተበጣጥሶ አሸባሪውን ለማንገስ ዳክረዋል።

ወርቅ በእሳት ነጥሮ ወርቅ እንደሚሆነው ሁሉ ኢትዮጵያም በፈተናዎቿ ነጥራ የምትወጣ እንጂ ጠላቶቻችን እንደሚያስቡት የምትፈረካከስ ሸክላ አይደለችም።

የጀግኖች አባቶቹ ልጆች የሆነው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን የተረከባትን ሉአላዊ ሀገር ከጠላት እና ከባንዳ ተከላክሎ ለቀጣዩ ትውልድ የማሸጋገር ታሪካዊ ኃላፊነት ያለበት ኃይል ነው።

ለዚህም ሠራዊታችን የገጠመንን ጠላት በማንኛውም ጊዜ እና ሠአት በመንግስት በሚሠጠው አቅጣጫ መሠረት ጠላትን በማደባየት ታሪካዊ ኃላፊነቱን ይወጣል።

#ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!!
316 views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 09:15:11 የአዳር መረጃ

የወገን ጥምር ጦር ራያ ቆቦ ወረዳን ለማስለቀቅ በተለያዩ የገጠር ቀበሌዎች እያደረገ ያለው የፀረ-ማጥቃት ውጊያ ዛሬም አዳሩን ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው:በህዝባዊ ማዕበል የገባው ሃይላቸውን እንደቅጠል ሲረግፍ ሌላ እልፍ ወራሪ እየመጣ ቢሆን በወገን ጦር እየተቆላ ነው::

ወልዲያ ከተማን ከጠላት ወረራ ለመከላከል እየተደረገ ያለው ውጊያም አመርቂ ውጤት እየተመዘገበበት ነው:በዶሮ ግብር ተራራዎች አቅጣጫ አቋርጦ ሲሪንቃ ላይ ዋናውን መንገድ ለመዝጋት ያደረገው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም: በታች በቃሊም በኩል አፍሪኬር ላይ ዋናውን አስፓልት ሊቆርጥ ያደረገው ሙከራም ሙሉ በሙሉ ተኮላሸቷል:በዚህ አቅጣጫ የመጣው አብዛኛው ሀይል እንደ ቅጠል የረገፈ ሲሆን የተረፈው ሀይል ደግሞ በሚጦ ቀበሌ አድርጎ ወደሗላ ፈርጥጧል:ይሄን ተከትሎም ወልዲያ ከተማ ዛሬም በወገን ጦር እጅ ነች::

አሸባሪው ቡድን የግዳኗን-ሙጃ ከተማ በመቆጣጠር ከዚያም ኩልመሰክን በመያዝ ከወልዲያ ላሊበላ ጋሸና የሚወሰደውን መሰመር ለመቁረጥ የነበረው እቅድም በወገን ጦር ብርቱ ከንድ ከሸፏል::

ሌላኛዋን የሰሜን ወሎ ከተማ ሀራን ለመውረር አሰፍሰፎ የሄደውና በድሬሮቃ ግንባር እየተፋለም የሚገኘው ቡድንም ነገሮች እንዳሰባቸው ቀላል አልሆነለትም::

በአጠቃላይ በወሎ ግንባር እየተካሄደ ባለው ጦርነት የወገን ጦር አሁናዊ ቁመና ጥሩ ሊባል የሚችል ነው:ምንም እንኳ ጦርነት በባህሪው በሰዓታትና በደቂቃዎች ልዩነት የሚፈጠረውን ለመገመት ቢያስቸግርም ለጊዜው ግን የወገን ጦር ተደራራቢ ድሎችን እያስመዘገበ ይገኛል::
326 views06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:50:22
የሶቬት ህብረት የመጨረሻው ፕሬዝዳንት ሚካይል ጎርባቼቭ በ91 ዓመታቸው አረፉ

የቀድሞው ሶቬት ህብረት የመጨሻው ፕሬዝዳንት ሚካይል ጎርባቼቭ በ91 ዓመታቸው ማረፋቸውን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ሰጥተውታል፡፡

ጎርቫቼቭ በከፍተኛ ህመም ሲሰቃዩ ቆይተው ትላንት አመሻሽ ማረፋቸው ነው የተገለጸው፡፡

የሩሲያው ፕሬዝዳት ቭላድሚር ፑን በሚካይል ጎርቫቼቭ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን መግለጻቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

የቀደሞዋ ሶቬት ህብረትን እ.አ.አ ከ1985-1991 የመሩት ሚካኤል ጎርባቼቭ በዓለም ሁለት ጎራ ተከፍሎ በነበረው 'ቀዝቃዛው ጦርነት' ምክንያት ሶቭየት ህብረት ከአሜሪካ የነበራትን ግንኙነት እንዲለዝብ ማድረግ ችለዋል ይባልላቸዋል።


ጎርባቼቭ ስልጣን ላይ እንደወጡ የሶቬት ህብረት መልሶ ግንባታ (perestroika) እና በተለይ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ግልጽነት (glasnost) እንዲሰፍን በሚል ያስተዋወቋቸው ማሻሻያ አዘል ፖሊሲዎቻቸው ዝነኛ አድርጓቸዋል፡፡

ጎርባቼቭ ከአሜሪካ አቻቸው ሮናልድ ሬገን ጋር የኒውክለር መሣሪያ የመቀነስ ስምምነት ማድረጋቸውም በሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ታሪክ ይታወሳል። ዓለም ላይ ርዕዮተ ዓለም ተኮር ጭምር የሆነው ቀዝቃዛው ጦርነትን ተከትሎ የኒውከለር ጦር መሳሪያ ስጋትን በማስወገዳቸው የሰላም ኖቤል ተሸላሚ ለመሆንም በቅተዋል፡፡

በሌላ በኩል ግን ጎርቫቼቭ በፕሬዝዳንትነት ዘመናቸው ምዕራባዊያንን አምነው የፈጸሟቸው ስህተቶች በወቅቱ ለተፈጠረው ለሶቬት ህብረት ወድቀት የአገሬው ዜጋ ጭምር ተጠያቂ ያደርጓቸዋል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል፡፡
317 views05:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 07:49:04
የቻይና ወታደሮች ለጋራ ወታደራዊ ልምምድ ሩሲያ ገቡ

በዚህ ሳምንት ሩሲያ በሚካሄደው የቮስቶክ 2022 ስትራቴጂካዊ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ የሚሳተፉ አገራት ወታደራዊ ቡድኖች ወደ ሩሲያ መድረሳቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ሰኞ ዕለት አስታውቋል።

ከሩሲያ ጦር ኃይሎች በተጨማሪ የቻይና, ቤላሩስ, አዘርባጃን, አርሜኒያ, ሶሪያ, ህንድ እና ሌሎች ተባባሪ አገራት ወታደሮች ይሳተፋሉ፡፡

በልምምዱ ከ50,000 በላይ ወታደሮች እና ከ5,000 በላይ የጦር መሳሪያዎች የሚያካትት ሲሆን 140 አውሮፕላኖች እና 60 የጦር መርከቦች, ጀልባዎች እና የድጋፍ መርከቦች በልምምዱ ይሳተፋሉ፡፡

ቮስቶክ-2022 የሚካሄደው እ.ኤ.አ በ1996 ሩሲያ፣ ካዛክስታን፣ ኪርጊስታን፣ ታጂኪስታን እና ቻይና በወታደራዊ ዘርፍ ያላቸውን በራስ መተማመን ለማሳደግ በገቡት ስምምነት መሰረት ነው፡፡
343 views04:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 07:37:29
መሰናበቻ መሰናበቻ
አሁን የቀረን ጌታቸው ብቻ

ወልዲያ
325 views04:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 23:41:55 ማምሻውን የኢትዮጵያ አየር ሃይል በመቀሌ ከተማ የተመረጡ ወታደራዊ ቦታዎችንና አንድ የነዳጅ ማከማቻን በመደብደብ ወራሪው የህወሓት ቡድን ላይ ከባድ ኪሳራ አድርሷል::
368 views20:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 23:19:22
ሰበር ዜና

የህውሃቱ ቁንጮ ጀኔራል ፍስሃ ኪዳኑ(ፍስሃ ማንጁስ) ወደ ማይቀርበት ሄዷል።

ነፍስ ይማር
393 views20:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:08:30 የዛሬው ውሎ

የወሎ ፋኖ ታሪክ ሰርቷል፣በርካታ የነፍስ ወከፍ እና የቡድን መሳሪያዎችን ማርኳል። ከ50 በላይ የህወሓት ታጣቂዎችን ማርኳል። በየግንባሩ ብዙ የተማረኩ አሉ።
አየር ሃይል ከቃሊም ተራራ ጀምሮ፣እስከ ቆቦ እና ዋጃ ጥሩ ስራ ሰርቷል።
መከላከያ የአማራ ልዩ ሀይል እና ሚሊሻው የተሰጠውን ግንባር በሚገባ መክቷል።
የወልድያ እናቶች በሙሉ አቅማችው ስንቅ ሲያዘጋጁ ውለዋል።ወጣቶች ግንባር ድረስ ስንቅ ሲያመላልሱ ውለዋል።
የትህነግ ቀንደኛ አዋጊ ጀነራል ሀየሎም ካህሳይ ከአፈር መቀላቀሉ ተሠምቷል
ህወሃት በራያ ግንባር ያሰለፈው የሀይል ብዛት ከ120ሺ በላይ ነው።
ነገር ግን ሰበር ዜና፣የድል ዜና ብዬ የምዘግበው ዘገባ የለም።
ምክንያቱም ጦርነቱ አሁንም አማራ ክልል ውስጥ ነው፣ እየተጎዳ እየተሰደደ እና እየተረሸነ ያለው የአማራ ህዝብ ነው።
ስለዚህ መዘናጋት ሳይኖር የህወሃትን ታጣቂ ከአማራ ክልል ለማስወጣት ብርቱ ድጋፍ እና ማስተባበር ከፊታችን ይጠበቅብናል።
የአማራ ህዝብ ሙሉ ለሙሉ ነፃ ሳይወጣ የድል ዜና የሚባል ማዘናጊያ የለም።

ውድ የቻናላችን ተከታዮች #Ethio_Today Facebook page ላይ መረጃዎችን ማጋራት ስላልቻልን ቴሌግራም ቻናላችንን #ሼር በማድረግ ተባበሩን

#Share

https://t.me/ethio2today
429 views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:56:35 ሰበር መረጃ


ወልዲያን አሰፍስፎ ለመቀራመት የመጣው የህውሃት ወራሪና ዘራፊ ኃይል በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣የአማራ ልዩ ሀይልና ፋኖ የተከፈተበት ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ የጣለውን ጥሎ ከአልውሃ ተጠቃሎ ሮቢትና አካባቢዋ መድረሱ ታውቋል።ጎብዬና አካባቢው በባለድሉ ጥምር ጦር ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።በሀራ በኩል ወደ ወርቄ ለመሄድ የነበረውም መቀልበሱን ሰምቻለሁ።የመረጃ ምንጮቼ እንደነገሩኝ ከሆነ ወደ ፊት የጥምር ጦሩ ፍጥነት ጨምሯል።በቅርቡ የምንሰማቸው አዳዲስ ጉዳዮች ይኖራሉ።ተከታትዬ አቀርባለሁ ህውሃት ወደ ጨለማ፣የትግራይ ህዝብ ወደ ብርሃን እየተጓዙ ነው ተደራጁ ደግፉ
Wasu Mohammed
419 viewsedited  17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 08:58:02
ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የአንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ህዝብ ኃላፊነት ያለበት ፤ በህገ-መንግስት የተመሠረተ በመንግስት የሚመራ፣ በማንኛውም ጊዜ እና ሁኔታ የሚሰጠውን ትዕዛዝ አክባሪ እና ፈፃሚ ፕሮፌሽናል ብሔራዊ ኃይል ነው።

ሠራዊታችን የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና የዜጎቿን ደህንነት የማረጋገጥ ታላቅና ታሪካዊ ኃላፊነት የተሸከመ ጀግና ነው።

ሠራዊታችን በማንኛውም ጊዜ፣ ቦታና ሁኔታ በመንግስት የሚሰጡ ትዕዛዞችን በህዝባዊነት፣ በጀግንነት እና በፅናት መከፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ ከፍሎ ተግባራዊ የሚያደርግ የድል ሠራዊት ነው።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት
204 viewsedited  05:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ