Get Mystery Box with random crypto!

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የኦንላይን (Online) ሙከራ ፈተና የሰጠው ት/ቤት ! በሀገር ደረጃ ለ | ሰበር !!

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የኦንላይን (Online) ሙከራ ፈተና የሰጠው ት/ቤት !

በሀገር ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የኦንላይን (Online) ሙከራ ፈተና መስጠቱን የአረካ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አስታዉቋል።

ይህም ሀገራዊ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች በፈተና ጊዜ የቴክኖሎጂ ችግር እንዳይገጥማቸው ያግዛል ነው የተባለው።

ፈተናው በሙክራ እየተሰጠ የሚገኘው ትምህርት ቤቱ #በራሱ_መምህር አማካኝነት በበለጸገው ሥርዓት አማካኝነት ነው።

የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ የዛሬው ተግባት እጅግ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።

የዚህን ትምህርት ቤት ተሞክሮ ወደ ሌሎች በዞን ወደሚገኙ ትምህርት ቤቶች በአጭር ጊዜ ለማስፋፋት እንደሚሰራ ገልጿል።

ይህ የኦንላይን (Online) ፈተና ዝግጅት ከማዳበር ባሻገር ለተማሪዎች የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩና እንድያጎለብቱ መልካም እድል መሆኑን ትምህርት ቤቱ አሳውቋል።

ትምህርት ቤቱ በዚህ ዘርፍ ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ዉጤታማ ለመሆን እየጣራ መሆኑን አመልክቷል።

ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት
  @Ethiiostudents_bot

        Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@Ethiio_Students  
@Ethiio_Students  
@Ethiio_Students  
╚═══════════╝