በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው የነበሩ እና በቅርቡ በምስራቅ ወለጋ፣ ጉቶ ጊዳ ወረዳ፣ አለልቱ ቀበሌ ወደሚገኘው መኖሪያ ስፍራቸው ለተመለሱ 800 ግለሰቦች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉን የዓለም ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) አስታውቋል ድጋፍ ከተደረጉት ቁሳቁሶች መካከል ሶላር የእጅ ባትሪዎች ፣ ጀሪካኖች ፣ የማዕድ ቤት እቃዎች ፣ ምንጣፎች ፣ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና መጠለያ እንደሚገኙበት ከድርጅቱ የተገኘው መረጃ ያሳያል። @Esat_tv1 @Esat_tv1 66.0K views09:35