Get Mystery Box with random crypto!

Ermi HD

የቴሌግራም ቻናል አርማ ermih — Ermi HD E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ermih — Ermi HD
የሰርጥ አድራሻ: @ermih
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.25K
የሰርጥ መግለጫ

This is the orginal chanal
Addmin✔✔(https://t.me/Ermi_HD)

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-03-19 15:14:11
1 መንፈስ ቅዱስ
2ከ መናፍስት ጋር የምናደርገው ውግያ በስጋ ያልሆነ ነው ለዚም
ወደ ኤፌሶን 6
12፤ መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።
13፤ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ።

14-15፤ እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤
16፤ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤
17፤ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው። ስለዚህ መንፈሳዊ ውግያ ነው ሰይጣንን እና የሱን መልእክተኞች የምንዋጋበት መሳርያ ነው ከሱም አንዱ ትልቁን ሰይጣን የምንዋጋበት መሳርያ ፆምና ፀሎት ነው ማቴ17
21፤ ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም፡ አላቸው። ውጤቱ ደግሞ ያው እግዚአቤሄርን መስለን ከጌታ ጋር መኖር እንዳለብን ማወቅና በመጨረሻም መንግስቱን መውረስ ነው ማቴ25
34፤ ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። 3ኛ ጥያቄ ግን አሜን ነው ሚባለው ጥያቄ ሳይሆን ቀጥታ የእግዚአብሄርን ቃል ነው የተጠቀሰው ማቴ5
9፤የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥
የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና። ምን ለማለት እንደፈለገም ግልፅ ነው ከእግዚአብሄር የተወለደ ክርሽስትያን በስራው የአባቱ ልጅ እንደሆነ የሚገልጥበት አንዱ መንገድ ማስታረቅ ነው።
1.7K viewsËrmï HD, 12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-07 19:17:29 https://chng.it/TwTwbHmh4M
2.0K viewsËrmï HD, 16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-06 15:48:26
“ የኢትዮጵያ ልጅ ሆይ! ልብ አድርገህ ተመልከት ኢትዮጵያ የተባለችው አንደኛ እናትህ ናት! ሁለተኛ ዘውድህ ናት! ሦስተኛ ሚስትህ ናት! አራተኛ ልጅህ ናት! አምስተኛ መቃብርህ ናት! እንግዲህ የእናት ፍቅር፣ የዘውድ ክብር፣ የሚስት ደግነት፣ የልጅ ደስታ፣ የመቃብር ከባቲነት እንደዚህ መሆኑን አውቀኸው ተነሳ!”
አፄው
1.7K viewsËrmï HD, 12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-06 22:26:45 ጆሮ ያለው ይስማ : ልብ ያለው ልብ ይበል

ይህ የበረኸኞች ቅዱሳን አባቶቻችን የንስሐ ግቡ ጥሪ ነው።


ቢያንስ ለ 21 የተዋህዶ ልጆች Share በማድረግ ክርስትያናዊ ግዴታችንን እንወጣ

ነገ ከባድ የመከራ ጊዜ አለና ዛሬውኑ ንስሐ ገብታችሁ ተዘጋጁ።

2012፣ 2013፣2014፣ የኢትዮጵያ የምጥ ዘመናት ናቸው።

ንስሐ ያልገባ በቶሎ ንስሐ ይግባ። ንስሐ የገባ ደግሞ በየሳምንቱ ለነፍስ አባቱ ራሱን ያስመርምር
የመዳን ቀን ዛሬ ነውና

በስንፍና ነገ ንስሀ እንገባለን ያላችሁ ነገ አባቶችን ላታገኙቸዉ ትችላላችሁ እና እንዳይረፍድባችሁ

ሥጋወደሙ የተቀበሉ፣ ንስሐ የገቡ ሰዎች ብቻ ጨለማውን ይሻገሩታል። ንጉሡ ከመምጣቱ በፊት አባጣ፣ ጎርባጣው የግድ መስተካከል አለበት። ተራራው ዝቅ ማለት አለበት። ጉድባው ጉድጓዱ መሙላት አለበት። በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር እስከ 2014 መጨረሻ ድረስ መከራው እንዲሁ
ይቀጥላል። ዘመኑ የምንጣሮ ዘመን ነው። ከኢትዮጵያ መከራ
ፍጻሜ በኋላ የመላዋ ዓለም መከራ ደግሞ ከዚያ በኋላ
ይጀምራል።

በቶሎ ንስሐ ገብታችሁ የታዘዛችሁትን ቀኖና ፈፀሙ ።

ዜጎች ቀን በቀን ይታረዳሉ ። አለቃው ይበዛል። አዛዥ እንጂ ታዛዥ አይኖርም። ሁሉ አለቃ፣ ሁሉ አዛዥ ይሆናል። ፍትሕና ሕግ ስፍራቸውን ለቀው ይሰደዳሉ። ትርምስምሱ ይወጣል። የሚያዝ የሚጨበጠው ይጠፋል። ክስ አድማጭ አይኖረውም። ወታደር ግራ ይጋባል። ዜጎች አማራጭ ያጣሉ። የውስጥም የውጪም ጠላቶች መግቢያ ቀዳዳው ይሰፋላቸዋል።

በአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያ ትወረራለች። ሰላም በማስከበር
በሚል ሰበብም በ2 ሃያላን ሀገራት የሚመሩ ሰባት የሙስሊም ሀገራት በኢትዮጵያ ምድር ላይ እሳት ያዘንባሉ። በአሰብ ወደብ ላይ በልዩ ሁኔታ የተከማቸው የጦር መሣሪያ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እንደበረዶ ይዘንባል። ብዙ ፍጅትም ይሆናል።
ኦርቶዶክሳውያን በያሉበት፣ በየተገኙበት እንደከብት ይታረዳሉ። የኢትዮጵያ ምድር በደም ትጨቀያለች። የደም ጎርፍ፣ የደም አበላ በምድሪቱ ላይ ይፈሳል ።

ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

ክፉ ረሃብ በኢትዮጵያ
ይመጣል። የሚበላ የሚጠጣ ከምድሪቱ ይጠፋል። ከጦርነቱ
የተረፈውን ህዝብ ረሃብ ይፈጀዋል። በስደት ምክንያት የዐቢይ ጾም የማይጾምበት ጊዜም ይመጣል። በረሃቡ ጊዜ ግን ጥቂቶችን የመትረፊያ ገዳማት ግን አሉ። ሰው የሚተርፍባቸው ገዳማትና አድባራት አሉ። ታቦተ ኢየሱስ ያለባቸው ገዳማትና አድባራት በሙሉ ሰው ይተርፍባቸዋል። በጊዜው እስከ አሁን ዝግ
የሆኑ ዋሻዎች ይከፈታሉ። የሚተርፉ ኢትዮጵያውያንም በዚያ
ይጠለላሉ። ከአሁኑ ጨውና የማይነቅዙ እህሎች አከማቹ።

ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

ከዚያም ክፉ በሽታ ይመጣል። ክፉ ወረርሽኝ ይከሰታል። ወረርሽኙ የ12 ሁለት ሰዓት ዕድሜ ብቻ የሚሰጥ ክፉ በሽታ ሲሆን ይኼም ጦርነቱንና ረሃቡን ተከትሎ ይመጣል።

መፍትሄው ንስሐ መግባት፣ ሥጋወደሙ መቀበል ነው።

አባቶች እንዲህ አሉ: ነገ ንስሐህን የሚቀበል ካህንም ላታገኙ
ትችላላችሁና ይሄን መልእክት የማንበብ ዕድል የገጠማችሁ
ልጆቻችን ሆይ ጨርቄን፣ ማቄን፣ ሳትሉ፣ ወገቤን ደረቴን ሳትሉ፣
ምክንያት ሳትደረድሩ፣ ዕለቱኑ ዛሬውኑ ንስሐ ግቡ።

ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

2015 በዘመነ ሉቃስ ንጉሱ ይመጣል። ለሳምንት ዝናብ ይዘንባል። የፈሰሰውን ደም አጥቦ ያስወግዳል። ምድር ትባረካለች።
የተረፉት ሰዎች እርስ በእርስ ይፈቃቀራሉ። ጠማማ ሰው አይኖርም። ንጉሱ ቴዎድሮስ በፍቅር ለ40 ዓመታት ይመራል።

በመላው ኢትዮጵያ የምትኖሩ ልጆቻችን ሆይ እነሆ አስቀድሞ በአባቶቻችን የተነገረው ሊፈፀም ግድ ነውና ልብ ያለው ልብ ይበል። በሗለኛው ጊዜ አልሰማንም : አላየንም እንዳትሉ እነሆ ከመከራው አስቀድሞ ይህ መልዕክት ከብዙ በጥቂቱ ለአእምሮ በሚመጥን ልብን በሚገዛ መልኩ ለመላው ህዝበ ክርስቲያን አስተላልፈናል።

በጸሎት የምንለምንና የምንማልድ ሁላችንንም በሰላም በመንፈስ ይጠብቀን ፍቅርንም ይስጠን ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን ፈቃዱም ሆኖ ጸሎታችንን ይቀበል ዘንድ ቀርበን እግዚአብሔርን እንለምነው!
ዐውቀን በሃብቱ እናድግ ዘንድ በእርሱም ስም እንመካ
ዘንድ...በነቢያት በሐዋርያትም መሰረት ላይ እንታነጽ ዘንድ
እንግዲህ በመንፈስ ቅዱስ እንነሳ!
ቀርበን አምላካችን እግዚአብሔርን እንለምነው ወዶ ጸሎታችንን
ይቀበል ዘንድ። አሜን!

ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

ቅዱስ አባ ዘወንጌል፣ ፍካሬ ኢየሱስ፣ ራዕየ ባሮክ ፣
የአባቶች ትንቢት


Share share share share share share

1 ሰው ለ 21 ምዕመን

ለመላው ህዝበ ክርስትያን መልዕክቱ እንዲደርስ በማድረግ የአባቶቻችንን አደራ እንወጣ

ጆሮ ያለው ይስማ : ልብ ያለው ልብ ይበል

መንግስተ ሰማያት ቀርባለች እና ንስሐ ግቡ

ውድድርሙኒ አስሙናኤል 21፣ ለምለምሊጊኖን 21 አካ ክስብኤል ቤቃ ጼቃ ሴቃ አልፋ ወኦ ቤጣ የውጣ ዮድ አህያ ሸራህያ ኤልሻዳይ ጸባዖት አማኑኤል እልመክኑን 21 .......
ብሮ ይህ መልእክት ሲላክ በብይ ተመርጦ ኢትዮጵያ ሰላም ናት በሚባል ሰአት ነው
4.7K viewsËrmï HD, 19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 11:09:08
ይሄ ሰው አምላኩን ነው እንዴ የተሸከመው??? ታቦት አምላክ ነው እንዴ?? እውነት የነሱ አምላክ ታቦት ለሙሴ ሲሰጥ አምላክህ ነው ብሉ ነው እንዴ??
ኦሪት ዘጸአት 25
10፤ ከግራር እንጨትም ታቦትን ይሥሩ፤ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፥ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ይሁን። ኢያሱና ሽማግሌዎቹስ በታቦት ፊት ስለሰገዱ አመለኩት ማለት ነው? መጽሐፈ ኢያሱ 7
6፤ ኢያሱም ልብሱን ቀደደ፥ እርሱና የእስራኤልም ሽማግሌዎች በእግዚአብሔር ታቦት ፊት እስከ ማታ ድረስ በግምባራቸው ተደፉ፤ በራሳቸውም ላይ ትቢያ ነሰነሱ። ሲጀመር ኢሄ ማወናበጃቸው ነው እንጂ ምንም የሚያገናኛቸው ነገር የለም ልክ ታቦት አምላክ ተደርጎ የተሰጠ ይመስል ዝም ብለው አምላክ አምላክ ይላሉ ሲቀጥል ታቦት አይደለም በምድር በሰማይም አለ አለማንበባቸው እና አለማመናቸው እንጂ ይህም በአዲስ ኪዳን መፅሀፍ የዮሐንስ ራእይ 11
19፤ በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፥ የኪዳኑም ታቦት በመቅደሱ ታየ፥ መብረቅና ድምፅም ነጐድጓድም የምድርም መናወጥ ታላቅም በረዶ ሆነ። ልክ እኔ ለምሳሌ ምንም ሳታረጊ አንቺ ጠንቁአይ ቤት ትሄጃለሽ ብዬ እራሴ ፈጥሬ ነግሬሽ ለራስሽ ቀድሞም የማትሄጂበትን ጠንቁአይ ቤት አትሂጂ ብሎ እንደመምከር ነው ወይም ላንቺ የኔ አምላክ ፈጣሪ እንጂ ተፈጣሪ አይደለም ብዬ እንደመናገር ነው... ኢሄ እኮ የሀይማኖት ፖለቲከኞች የሚሰሩአት ፕሮፖጋንዳ ነች የማያውቀውን ሰዎ ለማሳት እና ጣጣ የለውም ማንኛውም ጥያቄ ኬለሽ anytime መጠየቅ ትችያለሽ
1.4K viewsËrmï HD, 08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-17 21:39:39
#Hosaena

ቤተክርስቲያኒቱ ለ40 ዓመታት ስታቀርብ የነበረው ጥያቄ ተመለሰላት።

የሆሳዕና ከተማ የጥምቀት እና የመስቀል ደመራ ማክበሪያ ቦታ ምላሽ ማግኘቱን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ፅ/ቤት በዛሬው ዕለት አሳውቋል።

ቤተክርስቲያኒቱ ከጥንት ጀምሮ ስትጠቀምበት የነበረውን የባህረ ጥምቀት እና የመስቀል ደመራ በዓል ማክበሪያ ቦታ ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲያገኝ ከ1974 ዓ/ም ጀምሮ በየደረጃው ለሚገኙ የመንግስት አካላት ጥያቄ ስታቀርብ መቆየቷን ፅ/ቤቱ አስታውሷል።

ነገር ግን ጥያቄው ምላሽ ባለማግኘቱ እና ቦታውም ለሌላ ማህበራዊ አግልግሎት እንዲውል በመደረጉ በቦታው ላይ የአደባባይ በዓላቶች ማክበር የማያስችሉ በርካታ ችግሮች በመፈጠራቸው ቤተክርስቲያኒቱ ከ2011 ዓ/ም ጀምሮ የአደባባይ በዓላቶቿን ማክበር ሳትችል መቅረቷ ተገልጿል።

በመጨረሻም ለ40 ዓመታት ሲቀርብ የነበረው ጥያቄ የደቡብ ክልል መንግስት ፣ የሀዲያ ዞን እና የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ለችግሩ ትኩረት በመስጠት ባደረጉት ጥረት ለጥያቄው ተገቢው ምላሽ መሰጠቱን የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ፅ/ቤት ዛሬ አሳውቋል።

ቤተክርስቲያኒቱ ፥ የ2014 ዓ/ም የጥምቀት በዓልን ምዕመናን በጋራ እንዲያከብሩ ጥሪዋን አቅርባለች።

@tikvahethiopia
1.2K viewsËrmï HD, 18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ