Get Mystery Box with random crypto!

Egziabher Meslene እግዚአብሔር ምስሌነ

የቴሌግራም ቻናል አርማ emislene — Egziabher Meslene እግዚአብሔር ምስሌነ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ emislene — Egziabher Meslene እግዚአብሔር ምስሌነ
የሰርጥ አድራሻ: @emislene
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.57K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ይፋዊ የደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ካቴድራል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ት/ቤት ገጽ ነው፡፡
በዚህ ገጽ
- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት የጠበቁ ትምህርቶችን እናሰራጫለን፡፡
- የቅድስት ቤተክስቲያናችን እና የሰንበት ት/ቤቱን እንቅስቃሴ ወቅታዊ መረጃ እናደርስበታለን፡፡
ገጹን ለሌሎችም እያጋራችሁ የቤተክርስቲያናችንን አገልግሎት እናፋጥን፡፡ @EMislene_28Bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-05 06:24:28 "እውነተኛ ክርስቲያን አባቱ ክርስቶስን ይመስላል፡፡ ይሰደዳል እንጂ አያሳድድም፡፡ ይሰደባል እንጂ አይሳደብም፡፡ የጠፉትን ፍለጋ ይደክማል እንጂ ይባስ ብሎ አይገፈትርም፡፡ በወንድሙ ውድቀት ያለቅሳል እንጂ አይደሰትም፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን አባቱ ሌላ ነው፡፡

ለእግዚአብሔር የምናቀርበው ምስጋና በጊዜውም ያለ ጊዜውም ሊሆን ይገባል፡፡ ባገኘን ጊዜ ብቻ ሳይሆን ባጣንም ጊዜ፤ ባለጤና በሆንን ጊዜ ብቻ ሳይሆን በታመምንም ጊዜ፤ ሲሳካልን ብቻ ሳይሆን ባልተሳካልንም ጊዜ ማመስገን መለማመድ አለብን፡፡ የምስጋናችን ምንጭ የሁኔታዎች መለዋወጥ ሳይሆን ስለ አምላካችን ብቻ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ይህን ማድረግ ስንለማመድ በክብር ላይ ክብር ይጨመርልናል፤ እንደ አባታችን ኢዮብ የዲያብሎስን አፍ እንዘጋለን፡፡

ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን?” እንኪያስ "በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፡፡ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፡፡ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፡፡ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፡፡ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፡፡ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ዩቲዩብ ቻናል➠ https://m.youtube.com/channel/UCNjEKBSeBmsSGrHdlN3aSpQ
ፌስቡክ ገጽ➠https://m.facebook.com/EMislene
ቴሌግራም ቻናል➠ https://t.me/EMislene
ኢንስተግራም➠https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
ቲክቶክ ➠ https://vm.tiktok.com/ZMdm9g2TR
ድረ ገጽ➠ https://www.debregelila.org
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
1.2K views03:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 14:21:47 ጭንቅላቱ ዞሯል

የቄራ ሞተረኞች ወግ ነው :-

አንድ ወጣት ሞተረኛ በአንድ ምሽት ከከተማ እየወጣ ነው፡፡ ጭር ባለ አስፋልት ላይ እንደ ጀት እየበረረ ላሰበበት ቀጠሮ ለመድረስ ይከንፋል፡፡ ምንም እንኳን ጃኬት ደርቦ ቢለብስም ከፊት ለፊቱ የሚመጣው ነፋስ ደረቱንና ፊቱን እየገረፈው ተቸገረ፡፡ የለበሰው ጃኬት ደግሞ ከበስተኋላው ፈር ያለው ስለነበር ይሞቃል፡፡ ከፊት ግን ከምንም ሊያስጥለው አልቻለም፡፡ ምርር ሲለው ሞተሩን ከመንገድ ዳር ሱቅ አጠገብ አቆመ፡፡ ጃኬቱን አውልቆ አዙሮ ለበሰና አንዱን ጎረምሳ ‘እባክህ የጃኬቴን ዚፕ ከጀርባ ዝጋልኝ’ አለው፡፡ ጎረምሳው እሺ ብሎ ዞሮ የተለበሰውን ጃኬት እስከ ላይ ድረስ ግጥም አድርጎ ዘጋለት፡፡

አሁን ነፋሱ ደረቱን አይመታውም፡፡ ስለዚህ በላቀ ፍጥነት መብረር ጀመረ፡፡ ከከተማ ከወጣ በኋላ የበለጠ መክነፍ ጀመረ፡፡ ድንገት ግን ከፊቱ ደርቦ ለማለፍ የሚሞክር መኪና ብቅ አለበት፡፡ ራሱን ለማዳን ከመንገዱ ወጥቶ ሲበርር ሞተሩ ከቁጥጥሩ ውጪ ነበርና ተወርውሮ ከገደል ማዶ ያለ እርሻ ውስጥ ወደቀ፡፡ ከዚያ የሆነውን አያስታውስም፡፡ በዚያ ጨለማ እርሻ መካከል የሞተር ጩኸት የሰሙ ሰዎች ወደ ሥፍራው በሩጫ ሲደርሱ ሞተሩ በአንድ ወገን ሞተረኛው በሌላ ወገን ወድቀዋል፡፡ ተጯጯኹ፡፡ በዚያ ጨለማ ወጣቱን ከወደቀበት ሊያነሱት ተረባረቡ፡፡
‘ተርፎ ይሆን? አዪ የሰው ነገር’’
‘ምን አስሮጠው እስቲ!’’
‘ይሄ ሞተር ካልተከለከለማ መች ሰው ይተርፋል?’’
‘ኸረ እስቲ ወሬውን ትታችሁ ሆስፒታል ውሰዱት ‘
ቦታው በጫጫታ ተናወጸ።
በዚህ መካከል አንዱ በጨለማም ቢሆን የተጎጂውን አለባበስ አተኩሮ አየና ‘ኸረ ጭንቅላቱ ዞሮአል!’’ ብሎ ጮኸ ‘አዎ ዞሮአል አንተ እንዴት ቢወድቅ ነው ተባባሉ’’ አንዱ ወጣት እስቲ ከተስተካከለ ብሎ ተቻኩሎ አንገቱን ለማዞር ሲታገልም ምስኪኑን ሞተረኛ አንገቱን ቀጨው!
ነገሩ ያስቅም ያሳዝንም ይሆናል :: "ጭንቅላቱ ዞሯል" ብሎ መቅጨት ግን በሀገር የመጣ ችግራችን ይመስለኛል፡፡
ሰዎች በራሳቸው አስተሳሰብ ፣ አመለካከት ልክ ሆነው ሳለ እኛን ስላልመሰሉ ብቻ በግድ አዙረን የምንቀጫቸው ብዙ ናቸው፡፡ አንድ ሰው በአንተ አቅጣጫ ስላልዞረ : አንተ ያልከውን ስላላለ ብቻ ተሳስቷል ማለት አይደለም፡፡ አንተ የወደድከውን ስላልወደደ ፣ አንተ የጠላከውን ስላልጠላ ተሳስቷል ብለህ በግድ ልትቀጨው መሞከር የለብህም፡፡
"ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ" የሚለው አዋጅ አልፎ አልፎ ወደ ምዕራብም ወደ ሰሜንም ወደ ደቡብም ማየት አንደሚቻል ያሳያል:: ለተለያዩ አቅጣጫዎች ክፍት መሆን የግድ ነው::
የነጻነት ታጋዩ ኔልሰን ማንዴላ ፕሬዝዳንት ከሆኑ በኋላ በአሜሪካን ሀገር ባደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝት ወቅት በኒውዮርክ ሲቲ ኮሌጅ አዳራሽ ይፋዊ ቃለ መጠይቅ ላይ ለአንድ ጋዜጠኛ የሰጡት መልስ አይረሳኝም፡፡
ጋዜጠኛው ‘እንደ ፍልስጤሙ ያሲን አረፋት ፣ ጋዳፊ ፣ ካስትሮ ያሉ በጨቋኝነታቸው የታወቁ ሰዎች ጋር ወዳጅነት ያሳያሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች የደቡብ አፍሪካ መሪ ቢሆኑ ደስ ይልዎታል ወይ?’’ ብሎ ጠየቃቸው፡፡ኔልሰን ማንዴላ ዘና ብለው የተናገሩት የመጀመሪያ ዐረፍተ ነገር ሕዝቡን አስቁሞ ያስጨበጨበ ነበር፡፡
‘አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ከሚሠሯቸው ስኅተቶች አንዱ የእነርሱ ጠላቶች የእኛም ጠላቶች መሆን አለባቸው ብለው ማመናቸው ነው’’ እኛ የጠላነውን ያልጠላ ፣ እኛ የደገፍነውን ያልደገፈ ሰው ማንጓጠጥ የእኛ ሀገር አንዱ ሕመም ነው፡፡ እኛ የወደድነውን የቀለም ዓይነት ፣ እኛ የለበስነውን አለባበስ ፣ እኛ የምንወደውን ምግብ ፣ የእኛን አስተዳደግና ባሕል ሳይቀር ካልተከተለ በንቀት እንፈርጀዋለን፡፡ እኛ ካሰብነው አቅጣጫ ውልፍት ያለ ሲመስለን ጭንቅላቱ ዞሯል ብለን የምንቀጨው ብዙ ሰው አለ፡፡
አንድን ነገር ስንደግፍም ስንቃወምም እስከ ጥግ ነው፡፡ የወደድነውን ወገን ስናመሰግን የፈጣሪ ያህል እንከን አልባ አድርገን ነው [ፈጣሪ እንኳን በትሕትና ‘ኑ እንዋቀስ’ ‘እስቲ ፍረዱ! ያላደረግኩት ምን አለ?’ ብሏል] ፣ የጠላነውን ስናንኳስስ ደግሞ ትንሣኤ እንዳይኖረው አድርገን ነው፡፡ ስለዚህ በእኛ ሀገር ወይ ጠላት ወይ ወዳጅ ከሚል ውጪ ምንም የሥራ መደብ የለም፡፡ ሚዛናዊነት ፣
ግሬይ ዞን ፣ ‘አንተም ተው አንተም ተው’ ብሎ ነገር ሥፍራ አጥቷል፡፡ መሃል ሰፋሪ በሁለት ጥይት ይሞታል የሚለው ድሮ የቀረ ነው፡፡ በአሁን ዘመን አካሄድ መሃል ሰፋሪ በላውንቸር ይሞታል፡፡
የአጼ ኃይለ ሥላሴ ንጉሣዊ ቤተሰብ አባል የሆኑት ልዑል አስፋ ወሰን አስፋ ወሰን ዐሥራት ለአንድ የጀርመን ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲናገሩ ‘ከሁለት ሺህ የአፍሪካ ቋንቋዎች ውስጥ Opponent ለሚለው ቃል ተስተካካይ ትርጉም ያለው ቃል የለም፡፡ አፍሪካውያን የምናውቀው ወይ ወዳጅ ፣ ወይ ጠላት ነው እንጂ በሁለቱ መካከል ላለ ሰው መጥሪያ ስም እንኳን የለንም’ ብለው አስደንቀውኝ ነበር፡፡ እርግጥ ነው ቃል እንኳን አናጣም ብለን መሟገታችን አይቀርም፡፡ በተግባር ግን ከወዳጅና ጠላት በቀር መካከል ላይ ላለ ሰው ሥፍራ የለንም፡፡ ወይ እኛ ወደ ገመትነው አቅጣጫ መዞር አለበት፡፡ አለዚያም ጭንቅላቱ ዞሯል ብለን
እንቀጨዋለን፡፡
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

ዩቲዩብ ቻናል➠ https://m.youtube.com/channel/UCNjEKBSeBmsSGrHdlN3aSpQ
ፌስቡክ ገጽ➠https://m.facebook.com/EMislene
ቴሌግራም ቻናል➠ https://t.me/EMislene
ኢንስተግራም➠https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
ቲክቶክ ➠ https://vm.tiktok.com/ZMdm9g2TR
ድረ ገጽ➠ https://www.debregelila.org
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
1.5K viewsedited  11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 00:56:51
.

የክረምት የአስኳላ ትምህርት
ለ7ተኛ እና 8ተኛ ክፍል
ተማሪዎች

በደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ካቴድራል
እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ት/ቤት

የሚሰጡ የትምህርት
ዓይነቶች

• Mathematics
• Physics
• Chemistry
• Biology
• English
• Social Study
• Orthodox Life Skill


ከሰኞ - ዐርብ

በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ

ከ2:30 ጀምሮ

ሰኞ ሐምሌ 4 ትምህርቱ ይጀመራል።



"ኢንኅድግ ማኅበረነ እግዚአብሔር ምስሌነ"
ዩቲዩብ ቻናል➠ https://m.youtube.com/channel/UCNjEKBSeBmsSGrHdlN3aSpQ
ፌስቡክ ገጽ➠https://m.facebook.com/EMislene
ቴሌግራም ቻናል➠ https://t.me/EMislene
ኢንስተግራም➠https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
ቲክቶክ ➠ https://vm.tiktok.com/ZMdm9g2TR
ድረ ገጽ➠ https://www.debregelila.org
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
1.2K views21:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 18:54:39 የሕክምና ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር 10ኛውን የሕክምና ተልዕኳዊ ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ሰኔ 19/2014 ዓ.ም (June 26, 2022) ላይ አደረገ። የማኅበሩ የሕክምና ተልዕኮ ክፍል (Medical Missions Department) እንደገለጸው ይህ ለ2ኛ ጊዜ ወደ ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም የተደረገ ጉዞ ሲሆን የመጀመሪያውን ጉዞ መስከረም 9 ቀን 2014 ዓ.ም ላይ ማድረጉ ይታወሳል።

በዚህ የሕክምና ተልዕኮ ጉዞ፡-

♱ 49 ከተለያዩ ስፔሺያሊቲ የተውጣጡ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። ከነዚህ ውስጥም የውስጥ ደዌ፣ የዐይን፣ የጥርስ፣ የአንገት በላይ፣ የቆዳ ሐኪሞች፣ የህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች፣ ፋርማሲስቶችና ነርሶች ይገኙበታል።
♱ በአገልግሎቱም 242 ታካሚዎች ተጠቃሚ ሲሆኑ ገዳማውያን፣ የአብነት ት/ቤት መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ይገኙበታል።
♱ 178 ታካሚዎች የውስጥ ደዌ ሕክምና አግኝተዋል። 173 ታካሚዎች የዓይን ሕክምና ያገኙ ሲሆን 53ቱ የዓይን መነጸር ተጠቃሚ ሆነዋል። 33 ታካሚዎች የጥርስ ሕክምና ያገኙ ሲሆን 21 የጥርስ ነቀላ (Dental extraction) ተካሂዷል። 16 ታካሚዎች ከአንገት በላይ፣ 19 የቆዳ፣ እንዲሁም 10 ታካሚዎች የስነ-አዕምሮ ሕክምና አግኝተዋል።
♱ ለሁሉም ታካሚዎች መድኃኒቶች በነጻ ተሰጥተዋል
♱ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ለገዳሙ ተለግሰዋል
♱ የህብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች የአካባቢውን የጤና አጠባበቅ የዳሰሳ ቅኝት አካሂደዋል

ስለ ጽድቅ ብለው ዳዋ ጥሰው፤ ጤዛ ለብሰው፤ ድንጋይ ተንተርሰው፤ ማቅ ለብሰው፤ ግርማ ሌሊትን፣ ፀብ አጋንንትን፣ ድምፀ አራዊትን፣ ረሐቡንና ጥሙን ችለው፤ ዓለምን ንቀው፤ ከሰው ርቀው፤ በጾምና በጸሎት ተወስነው የሚኖሩትን አባቶችና እናቶች ማገልገል ምንኛ መታደል ነው?

በዚህ ታላቅ የበረከት አገልግሎት ላይ የተሳተፋችሁትን በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር በአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ስም እያመሰገነ ማኅበሩ በቀጣይ ሊሰራቸው ያሰባቸው ስራዎች የሁላችንንም ድጋፍ ስለሚሹ በልዑል እግዚአብሔር ስም አጋዥነታችሁ እንዳይለየን አደራ እንላለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር
ዩቲዩብ ቻናል➠ https://m.youtube.com/channel/UCNjEKBSeBmsSGrHdlN3aSpQ
ፌስቡክ ገጽ➠https://m.facebook.com/EMislene
ቴሌግራም ቻናል➠ https://t.me/EMislene
ኢንስተግራም➠https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
ቲክቶክ ➠ https://vm.tiktok.com/ZMdm9g2TR
ድረ ገጽ➠ https://www.debregelila.org
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
1.1K views15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 18:52:44
952 views15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 16:36:54 መልሱ የለም።

ክረምት ከሰኔ 26 - መስከረም 25

ዘመነ ክረምት ዘመነ ውኃ ማለት ነውና በዚኽ ዘመን ውኃ ይሠለጥናል፡፡

ውኃ አፈርን ያጥባል፣ እሳትን ያጠፋል፣ ቢኾንም በብሩኽነቱ ከእሳት፣ በቀዝቃዛነቱ ከነፋስ፣ በእርጥብነቱ ከመሬት ጋር ተስማምቶ ይኖራል፡፡ ክረምት በውስጡ አራት ወራትን (ሐምሌ፣ ነሐሴ፣ ጳጉሜንና መስከረምን) የያዘ ነው፡፡

ቅዱስ ያሬድ "ያረሁ ክረምተ በበዓመት፣ ይሰምዑ ቃሎ ደመናት፣ በየዓመቱ ክረምትን ያገባል፤ ደመናትም ቃሉን ይሰሙታል" ሲል በድጓው እንደነገረን የዘመናት ጌታ ልዑል እግዚአብሔር በየዓመቱ አዙሮ የሚያመጣልን ወቅት ነው፡፡

እያንዳንዱ ወቅት በውስጡ ዘጠና ዘጠና ቀናት ይዟል፡፡ ክረምት ግን ለብቻው 95 ቀናትን የያዘ ነው፡፡

ደመናትም ለቃሉ ትዕዛዝ ተገዢዎች በመኾን ዝናመ ምሕረቱን ጠለ በረከቱን የሚያወርዱበት ጊዜ ነው፡፡ ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25 ድረስ ሲሆን ነገ የምንጀምር ይሆናል።

ዩቲዩብ ቻናል➠ https://m.youtube.com/channel/UCNjEKBSeBmsSGrHdlN3aSpQ
ፌስቡክ ገጽ➠https://m.facebook.com/EMislene
ቴሌግራም ቻናል➠ https://t.me/EMislene
ኢንስተግራም➠https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
ቲክቶክ ➠ https://vm.tiktok.com/ZMdm9g2TR
ድረ ገጽ➠ https://www.debregelila.org
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
1.1K viewsedited  13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 19:53:23
ያረሁ ክረምተ በበዓመት፣ ይሰምዑ ቃሎ ደመናት፣ በየዓመቱ ክረምትን ያገባል፤ ደመናትም ቃሉን ይሰሙታል" ቅዱስ ያሬድ

ከሚከተሉት አማራጮች መካከል ስለ ዘመነ ክረምት ትክክል የሆነውን ይምረጡ።
Anonymous Quiz
12%
ክረምት ማለት ነፋስ የሚያይልበት ወቅት ማለት ነው።
6%
ዘመነ ክረምት የሚጀምረው ዝናብ በታየበት የመጀመርያው ሳምንት ላይ ነው።
19%
በኢትዮጵያ የጊዜ ቀመር አቆጣጠር መሰረት ሁሉም (4ቱም ) ወቅቶች 90 ቀናት አላቸው።
14%
ዘመነ ክረምት የሚጀምረው ሰኔ 26 ሲሆን መስከረም 1 ላይ ያበቃል።
21%
ሁሉም መልስ ናቸው።
28%
መልሱ የለም።
191 voters1.2K views16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ