Get Mystery Box with random crypto!

Egziabher Meslene እግዚአብሔር ምስሌነ

የቴሌግራም ቻናል አርማ emislene — Egziabher Meslene እግዚአብሔር ምስሌነ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ emislene — Egziabher Meslene እግዚአብሔር ምስሌነ
የሰርጥ አድራሻ: @emislene
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.57K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ይፋዊ የደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ካቴድራል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ት/ቤት ገጽ ነው፡፡
በዚህ ገጽ
- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት የጠበቁ ትምህርቶችን እናሰራጫለን፡፡
- የቅድስት ቤተክስቲያናችን እና የሰንበት ት/ቤቱን እንቅስቃሴ ወቅታዊ መረጃ እናደርስበታለን፡፡
ገጹን ለሌሎችም እያጋራችሁ የቤተክርስቲያናችንን አገልግሎት እናፋጥን፡፡ @EMislene_28Bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-26 20:47:33
"ክርስቶስ ሠምራ የአምላክ አገልጋይ
ይበራል ስምሽ ዛሬም በምድር ላይ"
ከሚከተሉት አማራጮች መካከል ስለ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ትክክል ያልኾነውን ምረጡ።
Anonymous Quiz
8%
እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በሕይወተ ስጋ ለ375 ዓመታት ኖራለች።
7%
ነሐሴ 24 የዕረፍት መታሰቢያ በዓሏ ሲኾን ግንቦት 12 ደግሞ በዓለ ልደቷ ይከበራል።
11%
ቅድስት እናታችን ለሰይጣን ምሕረትን ለምናለች።
2%
መቃብሯ ጓንጉት ደሴት ውስጥ ሲኾን በኋላም ስሙ ደብረ ምሕረት፡ ደብረ ፍቅር ተብሏል።
8%
እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በህግ ጋብቻ ያፈራቻቸው 11 ልጆች ነበሯት።
2%
ቅድስት እናታችን በቁመቷ ልክ ጉድጓድ አስቆፍራና የሎሚ እንጨት አስተክላ በውስጡ በመግባት ለብዙ አመታት ተጋድላለች።
1%
አማቷ ኢየሱስ ሞዓ ስለእርሷ " ለታላቅ ቁም ነገር የተመረጠች" ሲል ቀድሞ ትንቢትን ተናግሮ ነበር።
3%
በጣና ሐይቅ ውስጥ ገብታ ለ3 ዓመታት ጸልያለች።
53%
ቅድስት እናታችን ዜግነቷ ኢትዮጵያዊ አይደለም።
5%
ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ፡ መታሰቢያዋን ላደረገ ስሟን ለጠራና በስሟ በታነጸ ቤተክርስቲያን ቅጥር ለሚቀበር እስከ 10 ትውልድ ሊማርላት ቃልኪዳን ተገብቶላታል።
158 voters1.1K views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 09:01:01 ብሒለ አበው

‹ራስህን በሐሰት አትውቀስ ራስን መክሰስ ትህትና አይደለም ታላቁ ትህትና ሰዎች ሲወቅሱህ መታገስ ነው።›
/ቅዱስ ስራፕዮን/

‹‹የማታምንበትን ነገር ለሰው ስትል አትስራው ከሰራኸው እንደምትጠፋበት እወቅ።››
/መጽሐፈ ምክር/

‹‹አንደበቱን ከቧልት ከሐሜት ያየውንም ምሥጢር ከመናገር የሚከለክል ሰው ልቦናውን ከኀልዮ ኃጢአት ያርቀዋል።››
/አረጋዊ መንፈሳዊ/

‹‹ ጸጋ ቢሰጥህ በተሰጠህ ጸጋ አመስግን፡ ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እንዳታጣ።››
/ማር ይስሐቅ/

‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ጥበብ ይለየዋል።››
/አረጋዊ መንፈሳዊ/

‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።››
/አባ እንጦንስ/

‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻለን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻለናል?››
/ቅዱስ አትናቴዎስ/

‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ጸጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም። የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢአተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደነደደ ይኖራል።››
/ቅዱስ ሚናስ/

‹‹በማንም ላይ ክፋትን አትስሩ አትፍረዱ። ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና።››
/ታላቁ አባ መቃርስ/

‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናለሁ። በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም።››
/ቅዱስ አርሳንዮስ/

‹‹ቤተ ክርስቲያን መጠጊያችን ነች። ቤተ ክርስቲያን የኖኅ መርክብ ነች። በውስጧ እንጠለላለን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል።››
/ቅዱስ እንድርያስ/

‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከሆነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ፡ከበደል በንስሐ ንጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተሞላን እንሆናለን።››
/አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/

‹‹ሥጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ሕይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው።››
/ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/

‹‹የቤተ ክርስቲያን ሕይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ሕይወታችሁ ይልቅ የቤተ ክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ።››
/ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/

‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ጸሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትጸልይ እደር።››
/ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ/

‹‹ኃጢአታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል ፡ኃጢአታችንን እኛ ረስተን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።››
/ቅዱስ እንጦንስ/

በማኅበራዊ መገናኛዎቻችን ቤተሰብ ይሁኑ!
የዩቲዩብ ቻናል፡



የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMislene
የፌስቡክ ገጽ፡
https://www.facebook.com/EMislene/
የኢንስታግራም ገጽ፡
https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
የቲክቶክ ገጽ፡
https://www.tiktok.com/@egziabhermeslene28
ድሕረ ገጽ፡
www.debregelila.org
1.3K views06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 07:50:36

1.2K views04:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 07:23:53 ክርስቲያን መኾንህን በቃል ሳይኾን በተግባር አሳየኝ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ክርስቲያኖች ግን ክርስቲያኖች ለመኾናቸው መታወቅ የሚገባቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው ምሥጢራትን ሲቀበሉ ብቻ ሳይኾን የትም ቦታ በሚኖሩት የቅድስና ሕይወት ነው፡፡ በአፍአ የከበሩ ሰዎች በአፍአ ከሚያሳዩት ምልክት እንደሚታወቁ ኹሉ፥ እኛም ልንታወቅ የሚገባን በነፍሳችን ክብር ነው፡፡ በሌላ አገላለጥ አንድ ክርስቲያን መታወቅ ያለበት በተሰጠው ልጅነት ብቻ ሳይኾን ለልጅነቱ እንደሚገባ በሚያሳየው አዲስ ሕይወትም ጭምር ሊኾን ይገባል፡፡ ይህ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃንና ጨው ሊኾን ይገባዋል፡፡ ለዓለም ብርሃን መኾንህስ ይቅርና ለራስህ እንኳን ብርሃን መኾን ካልተቻለህ፣ የሚሰፋ ቁስልህን በዘይት ማሰርም ካቃተህ፥ ክርስቲያን መኾንህን የምናውቀው እንዴት ነው? ወደ ተቀደሰው ውኃ ገብተህ በመጠመቅህ ነውን? በዚህስ አይደለም ! ይህስ እንዲያውም ዕዳ ፍዳ ይኾንብሃል [እንጂ ክርስቲያን መኾንህን እንድናውቅህ አያደርገንም]፡፡ ይህ ሀብት (ልጅነት) ታላቅ ነውና ለዚህ ሀብት እንደሚገባ ለማይኖሩት ሰዎች ዕዳ ፍዳ መጨመሪያ ነው፡፡ አዎን፥ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃኑን ማብራት ያለበት ከእግዚአብሔር በተቀበለው ጸጋ ብቻ ሳይኾን እርሱ ራሱም ድርሻውን በመወጣት ነውና፡፡ ክርስቲያን ካልኾኑት ይልቅ በኹለንተናው - በአረማመዱ፣ በአተያዩ፣ በአለባበሱ፣ በአነጋገሩ - ብልጫ ሲኖረው ነውና፡፡ ይህንም የምለው ልጅነትን የተቀበሉ ክርስቲያኖች ልጅነትን ተቀበሉ በመባል ብቻ ሳይኾን የሌሎች ሰዎች ረብ ጥቅም ይኾን ዘንድ ለተቀበሉት ልጅነት የሚገባና ሥርዓት ያለው ሕይወት እንዲኖሩ ስለምሻ ነው፡፡

አሁን ግን ከሌሎች ከማያምኑት ብልጫ ኖሮህ እንዳየው በምፈልገው ሕይወት፥ በኹሉም ረገድ ተቃራኒ ኾነህ አይሃለሁ፡፡ ለምሳሌ ከቦታ አንጻር፥ ቀኑን ኹሉ የፈረስ እሽቅድምድምንና ተውኔትን፣ ነውርን የተሞሉ ትርኢቶችንና የክፉዎችን ማኅበር፣ ርኵሰትንም የተሞሉ ሰዎችን ስትመለከት እንደምትውል አይሃለሁ፡፡ ከፊትህ አንጻር፥ ዘወትር ያለ ልክና እንደ አመንዝራ ሴት ስትስቅ እመለከትሃለሁ፡፡ ከአለባበስህ አንጻር፥ ከተዋንያንና ጠቢባን ነን ከሚሉ ሰዎች ምንም እንደማትለይ አስተውልሃለሁ፡፡ ከሚከተሉህ ሰዎች አንጻር፥ ብዙ ውዳሴ ከንቱንና ሽንገላን እንደምትሻ አይሃለሁ፡፡ ከንግግርህ አንጻር፥ ምንም ደኅና ነገር፣ በቁዔት ያለው ቃል፣ ለሕይወታችን የሚረባ ንግግር እንደሌለብህ አደምጣለሁ፡፡ ከማዕድህ አንጻርም ከዚያ ጽኑዕ የኾነ ወቀሳ የሚያመጣብህ እንደ ኾነ አያለሁ፡፡

ታዲያ እስኪ ንገረኝ ! ክርስቲያንን ክርስቲያን ከሚያስብሉት ነገሮች እጅግ የራቅህ ኾነህ እያለ፥ ክርስቲያን መኾንህን መለየት የምችለው በምንድን ነው? ክርስቲያን መባልህስ ይቅርና፥ ሰው ብዬ ልጠራህ የምችለውስ እንዴት ነው? እንደ አህያ ትራገጣለህና፤ እንደ ኮርማ ትሴስናለህና፤ እንደ ፈረስ ከሴቶች ኋላ ኾነህ ታሽካካለህና፤ እንደ ድብ ሆዳም ነህና ፤ ሥጋህን እንደ በቅሎ ሥጋ ትሰገስጋለህና፤ እንደ ግመል ቂም ትይዛለህና፤ እንደ ተኵላ ትነጥቃለህና፤ እንደ እባብ ትቈጣለህና፤ እንደ ጊንጥ ትናደፋለህና፤ እንደ ቀበሮ ተንኰለኛ ነህና፤ እንደ እባብ ወይም እንደ እፉኝት በጕረሮህ መርዝ አለና፤ እንደ ክፉ ጋኔን ከወንድምህ ጋር ትጣላለህና፡፡ ታዲያ ክርስቲያን የሚለውስ ይቅርና፥ በምንህ ሰው ብዬ ልጥራህ? ሰው የሚያስብል ምልክት ሳይኖርህ እንዴት ብዬ ከሰው ዘንድ ልቊጠርህ? የንኡሰ ክርስቲያኖችና የክርስቲያኖች ልዩነት ባሰብሁ ጊዜ ልዩነቱ የሰውና የአርዌ ገዳም ያህል ይኾንብኛል፡፡ ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? አርዌ ገዳም ብዬ ልጥራህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጭካኔህ ከአራዊተ ገዳም በላይ ነውና፤ በሌላ መልኩ ደግሞ እነርሱ እንደዚያ የኾኑት ከተፈጥሮአቸው የተነሣ እንጂ እንደ አንተ ወደውና ፈቅደው አይደለምና፡፡

ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? ጋኔን ልበልህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጋኔን የሆድ ባሪያ አይደለምና፤ ፍቅረ ንዋይም የለበትምና፡፡ ታዲያ ከአራዊተ ገዳምም ከአጋንንትም የሚብስ ክፉ ግብር ከያዝህ፥ ንገረኝ - ሰው ብዬ እጠራህ ዘንድ ይገባኛልን? ሰው ለመባል እንኳን የሚበቃ ምግባር ከሌለህስ፥ ክርስቲያን ብለን ልንጠራህ የምንችለው እንዴት ነው?


ኢንኅድግ ማኅበረነ እግዚአብሔር ምስሌነ
እግዚአብሔር ምስሌነን መሰባሰባችን አንተው!


በማኅበራዊ መገናኛዎቻችን ቤተሰብ ይሁኑ!
የዩቲዩብ ቻናል፡



የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMislene
የፌስቡክ ገጽ፡
https://www.facebook.com/EMislene/
የኢንስታግራም ገጽ፡
https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
የቲክቶክ ገጽ፡
https://www.tiktok.com/@egziabhermeslene28
ድሕረ ገጽ፡
www.debregelila.org
1.1K views04:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 22:45:54
የቅድስት ኪዳነ ምህረት የንግስ በዓል
በደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ቤተ ክርስቲያን
በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።

“ሰላም ለአእዛንኪ እለ ተበሥራ ኪዳነ
እምአፈ ፈጣሪ ወልድኪ ዘባሕርየኪ ተከድነ
አምሕለኪ ማርያም ከመ ኢታርእዪኒ ደይነ
እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ
ቦኑ ለከንቱ ኪዳንኪ ኮነ ”

ባሕርይሽን ከተዋሐደ ከፈጣሪ ልጅሽ አንደበት የኪዳን ምሥራችን ለተበሠሩ ጆሮዎችሽ
ሰላምታ ይገባል፡፡
ያለምግባር የማልጸድቅማ ከሆነ
በውኑ ኪዳንሽ ለከንቱ ይሆናልና
ማርያም ሆይ
ፍርድን እንዳታሳዪኝ አምልሻለኊ።
__________________________
መ ል ክ ዐ ኪ ዳ ነ ምህረት

°•°•°•°•°•°•°•°°•°•°•°•°•°•°•°
በማኅበራዊ መገናኛዎቻችን ቤተሰብ ይሁኑ!
የዩቲዩብ ቻናል፡



የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMislene
የፌስቡክ ገጽ፡
https://www.facebook.com/EMislene/
የኢንስታግራም ገጽ፡
https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
የቲክቶክ ገጽ፡
https://www.tiktok.com/@egziabhermeslene28
ድሕረ ገጽ፡
www.debregelila.org
1.5K views19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 09:55:51 LIVE ON FACEBOOK
1.4K views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 20:59:15
ከሚከተሉት አማራጮች መካከል በያዝነው በወርኅ ሐምሌ ውስጥ የሚውሉ ዓመታዊ ክብረ በዓላት ያልሆነውን ለዩ።

ከረድኤትና ከበረከታቸው ያሳትፈን።
Anonymous Quiz
9%
ሐምሌ 5- ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወ ጳውሎስ
6%
ሐምሌ 6- ቅዱስ በርተሌሜዎስ ሐዋርያ
8%
ሐምሌ 7- አጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ
1%
ሐምሌ 8- አቡነ ኪሮስ ጻድቅ (አረጋዊና ገዳማዊ)
3%
ሐምሌ 10- ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
3%
ሐምሌ 14- ታላቁ ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት አለቃ)
8%
ሐምሌ 19- ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
3%
ሐምሌ 22- ቅዱስ ዑራኤል ሊቀመላእክት
4%
ሐምሌ 23- እናታችን ቅድስት መሪና
56%
መልሱ የለም ።
119 voters450 views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 10:44:22
ጸሐፊ - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፡ ትርጉም በገብረ እግዚአብሔር ኪደ።

የሽፋን ዋጋ- 150 ብር

የገጽ ብዛት - 199

ከመጽሐፉ የተወሰደ

ለእኛ (ለክርስቲያኖች) ምግባር መያዝ ግዴታ ነው፡፡ ምግባር ከሌለን ግን “ክርስቲያን” የሚለው ስም ለእኛ የሚፈይደው ምንም ነገር የለም፡፡ በዚህ ተደነቅህን? እንኪያስ ንገረኝ ! በዐውደ ውጊያ የማይሳተፍ፣ ለሚመግበው ንጉሥም የማይዋጋ ከሆነ አንድ ወታደር ወታደር ተብሎ ቢጠራ ምን ጥቅም አለው? ለንጉሡ ክብር የማይዋጋ ከሆነስ ወታደር ተብሎ ባይጠራ ይሻለዋል፡፡ ይህ ሰው በንጉሡ የሚመገብ ሆኖ እያለ፥ ነገር ግን ንጉሡ በጠላቱ ላይ ድል እንዲያደርግ የማይዋጋ ከሆነ እንዴት ከቅጣት ሊያመልጥ ይችላል? ንጉሡን ምሳሌ አድርጌ ልናገረው የፈለግሁትስ ምንድን ነው? ልለው የፈልግሁት እግዚአብሔር በትንሹ ስለገዛ ነፍሳችን እንድንጠነቀቅ (ምግባር መያዝ እንድንችል) ኃይል (አቅም) ሰጥቶናል ነው፡፡

ንባብ ኅሊናን በተመስጦ ሊሞላ የሚችል መንፈሳዊ ዘዴ ከመስጠቱም በላይ ተቃዋሚ አሳቦችን የሚያጠፋውንና እግዚአብሔርን መውደድ የሚያስችለውን ስሜት በልብ ውስጥ ያጎናጽፋል። አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ!

ባለፈው ሳምንት ምን አነበቡ? በዚህ ሳምንትስ ምን እያነበቡ ነው? ምንስ ሊያነቡ አስበዋል?

በማኅበራዊ መገናኛዎቻችን ቤተሰብ ይሁኑ!
የዩቲዩብ ቻናል፡



የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/EMislene
የፌስቡክ ገጽ፡
https://www.facebook.com/EMislene/
የኢንስታግራም ገጽ፡
https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
የቲክቶክ ገጽ፡
https://www.tiktok.com/@egziabhermeslene28
ድሕረ ገጽ፡
www.debregelila.org
675 views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 07:02:48 ሰኔ 30

የነቢይ፣ ሰማዕትና ሐዋርያ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ልደት

፦ ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው።

በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጎረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን "አይሆንም ዮሐንስ ይባል" አለች። "ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም" አሏት።

አባቱንም ጠቅሰው "ማን ሊባል ትወዳለህ" አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ "ዮሐንስ ይባል" ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ።

ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው።

ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና "ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት" አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ።

"የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምጽ እነሆ" ብሎ ኢያሳያስ የተናገረለት ይህ ነው። ሚልክያስም ስለርሱ እንዲህ አለ "በፊትህ ጎዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልአክተኛዬን እኔ እሰዳለሁ"።

ራሱ መድኃኒታችንም ስርሱ ሲናገር "ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም" ብሏል። ይህ የእግዚአብሔር ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና።

ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ። እኛንም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱም እኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ዩቲዩብ ቻናል➠ https://m.youtube.com/channel/UCNjEKBSeBmsSGrHdlN3aSpQ
ፌስቡክ ገጽ➠https://m.facebook.com/EMislene
ቴሌግራም ቻናል➠ https://t.me/EMislene
ኢንስተግራም➠https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
ቲክቶክ ➠ https://vm.tiktok.com/ZMdm9g2TR
ድረ ገጽ➠ https://www.debregelila.org
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
946 views04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 14:22:37
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሕይወት ዘመኑ ብዙውን ጊዜ ያሳለፈው በስደትና በእሥር ነበር። በተለይም በእርሱ ዘመን የነበረው አጼ ዳዊት አሣሥሮ አንገላቶትና አስገርፎት ነበር። ታዲያ አባ ጊዮርጊስ በእሥር ቤት እያለ አጼ ዳዊት ሞተ፡፡

የንጉሡን ሞት ለአባ ጊዮርጊስ ሰዎች መጥተው ነገሩት። አባ ጊዮርጊስም ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡ ሰዎቹም "ይኽ ንጉሥ ሲገርፍኽና ሲያሥርኽ አልነበረም ወይ? በመደሰት ፈንታ ለምን ታለቅስለታለኽ? "ብለው ጠየቁት፡፡

አባ ጊዮርጊስም "ሌላ እጥፍ ግርፋት እየጨመረልኝ ብዙ ዓመት ቢኖር ደስ ይለኝ ነበር! እመቤቴ ማርያምን ይወዳታል እኮ!" በማለት መለሰ፡፡

ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ዩቲዩብ ቻናል➠ https://m.youtube.com/channel/UCNjEKBSeBmsSGrHdlN3aSpQ
ፌስቡክ ገጽ➠https://m.facebook.com/EMislene
ቴሌግራም ቻናል➠ https://t.me/EMislene
ኢንስተግራም➠https://www.instagram.com/egziabher_meslene28/
ቲክቶክ ➠ https://vm.tiktok.com/ZMdm9g2TR
ድረ ገጽ➠ https://www.debregelila.org
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
977 views11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ