Get Mystery Box with random crypto!

elam

የቴሌግራም ቻናል አርማ elam12 — elam E
የቴሌግራም ቻናል አርማ elam12 — elam
የሰርጥ አድራሻ: @elam12
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.53K
የሰርጥ መግለጫ

የየሰንበቱ መዝሙር፣ ምስባክና ወንጌል
Elamaba.org

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-05 14:46:17 መዝሙር ዮም ንወድሳ ከነሐሴ ፩ - ነሐሴ ፯

(በ፩/ኒ) ዮም ንወድሳ ለማርያም በእንተ ዘተወልደ እምኔሃ መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ ፆረቶ በከርሣ ውእቱኒ ቀደሳ (መ) እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ አማን መላእክት ይኬልልዋ።
ትርጕም፦
ዛሬ (ኑ) ማርያምን እናመስግናት (ጌታችን) ከሷ ስለተወለደ በሚያስደንቅ ግርማ የልዑል ኃይል ጋረዳት በማኅፀኗ ወሰነችው እሱም አከበራት የሰንበት ጌታ የይቅርታ አባት በሚያስደንቅ ግርማ የልዑል ኃይል ጋረዳት በእውነት መላእክት ያመስግኗታል።
የዕለቱ ምንባባት፦
፩ቆሮ ፰፥፩ - ፍ፤
፩ጴጥ ፬፥፩ - ፮፤
ግብ ፳፮፥፩ - ፳፬፤
ወንጌል፦ ማቴ ፲፪፥፴፰ - ፍጻሜ፤
ቅዳሴ - ዘእግዝእትነ ማርያም
የዕለቱ ምስባክ፦
እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ፤
ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ፤
ወውእቱ ልዑል ሣረራ። መዝ ፹፮፥፭
ትርጕም፦
ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፤
በውስጧ ሰው ተወለደ፤
እርሱ ራሱ ልዑል መሠረታት።
ምሥጢር፦
ሰው ሁሉ ቤተ መቅደስ እናታችን እግዚአብሔር አባታችን ይላል፤
ተወልደ በውስቴታ ይነግሥ በውስቴታ ሲል ነው። ሕዝቅያስ በኢየሩሳሌም ተወልዶ በኢየሩሳሌም ይነግሣል አንድም ዘሩባቤል በባቢሎን ተወልዶ በኢየሩሳሌም ይነግሣል፤
ልዑል እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን በረድኤት አጸናት፤
አንድም በጸጋ ከሥላሴ የተወለደ ሰው ሁሉ እመቤታችን፤ ቤተክርስቲያን እናታችን እግዚአብሔር ወልድ አባታችን ይላል፤
ጌታ ከእመቤታችን ተፀነሰ ፅንሱን ልደት ልደቱን ፅንስ ይለዋልና አንድም በሥጋ ተወለደ አንድም ምእመናን ከቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ልደትን ተወለዱ፤
እግዚአብሔር እመቤታችንን በንጽሕና በቅድስና አጸናት ማለት እንድትችለው አደረጋት አንድም ቤተ ክርስቲያንን በደሙ አከበራት።
890 views11:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 00:52:20

388 views21:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 00:50:37

391 views21:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 16:20:22 መዝሙር በሰንበት ቦአ ከሐምሌ ፳፬ እስከ ሐምሌ ፴

(በ፫/ሙ) በሰንበት ቦአ ኢየሱስ ምኵራቦሙ ለአይሁድ ምህሮሙ ወይቤሎሙ አክብሩ ሰንበትየ (በ) በሰንበት አጋንንተ አውጽአ ወበቃሉ እለ ለምፅ አንጽሐ (በ) በሰንበት ወረቀ ምድረ ወገብረ ፅቡረ ወበምራቁ አሕየወ ዕውረ (በ) ዘይኤዝዞሙ ለደመናት ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር (በ) ያውርዱ ዝናመ ውስተ ኵሉ ምድር ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን (በ) ውስተ ፍና ኀበ ይትፈቀድ መካን ከመ ኅቡረ ይትፈሣሕ ዘይዘርዕ ወየዓርር (በ) ምድርኒ ርእየቶ ወአእኰተቶ ባሕርኒ ሰገደት ሎቱ።

ትርጕም፦

በሰንበት ወደአይሁድ ምኲራብ ገባ ሰንበቴን አክብሩ ብሎ አስተማራቸው በሰንበት አጋንንትን አወጣ በቃሉ ለምፃሞችን አነጻ በሰንበት ምራቁን ወደምድር እንትፍ አለ ጭቃም አደረገ በምራቁ ዕውሩን አዳነ በምድር ሁሉ ላይ ዝናምን ያወርዱ ዘንድ ደመናዎችን የሚያዛቸው እሱ ነው በሚያስፈልግበት ስፍራ ሁሉ። የሚዘራም የሚያጭድም አንድ ላይ ይደሰቱ ዘንድ። ምድር አየችው አመሰገነችው ባሕርም ሰገደችለት።

የዕለቱ ምንባባት፦
፪ቆሮ ፲፥፩ - ፍ፤
ያዕ ፫፥፩ - ፱፤
ግብ ፳፰፥፲፯ - ፍ፤

የዕለቱ ወንጌል፦ ማር፮፥፵፯ - ፍ ወይም ማቴ ፰፥፳፫ - ፍጻሜ

ቅዳሴ ፡- ዘኤጲፋንዮስ ወይም ዘእግዚእነ፤

የዕለቱ ምስባክ፦

ያዐርግ ደመናተ እምአጽናፈ ምድር፤
ወገብረ መብረቀ ለጊዜ ዝናም፤
ዘያወጽኦሙ ለነፋሳት እመዛግብቲሆሙ። መዝ ፻፴፬፥፯፤

ትርጕም፦

ከምድር ዳር ደመናትን ያወጣል
ለዝናም ጊዜም መብረቅን አደረገ፤
ነፋሳትን ከመዛግብቱ ያወጣል።

ምሥጢር፦

ደመናትን ከጽንፈ ምድር ፈጠረ።
የደመናትን ተፈጥሮ ከዚህ ይናገሩታል። ከዚህ እስከ ብሩህ ሰማይ ውኃ መልቶ ነበርና ለይትጋባእ ማይ ውስተ ምዕላዲሁ - ውኃ በመከማቻው ይሰብሰብ ብሎ ከሦስት ከፍሎታል ምድርም ደም እንደሰረበው ጉበት ሆና ታየች አሥራ ሁለቱን ነፋሳት አውጥቶ አስመታት ጸጥ አለች (ስምንቱ የመዓት ሲባሉ አራቱ የምሕረት ናቸው) በዚህ ጊዜ ከይቡስ ምድር ይቡስ ጢስ ከርጡብ ባሕር ርጡብ ጢስ ወጥቶ አንድ ደመና ይሆናል ወይመውቁ በፀሐይ ወይከውኑ ክልኤሆሙ አሐደ ደመና - በፀሐይ ይሞቃሉ አንድ ደመና ይሆናሉ እንዲል።
መብረቅን ለዝናም ምልክት አደረገ አንድም ለዝናም ምልክት የሚሆን መብረቅን ፈጠረ። ይኸውም ለከንቱ አይደለም አትክልት አዝርዕት ሊያብቡባቸው ሊያፈሩባቸው ነው። ወይበርቁ መባርቅት ለጽጋብ ወለበረከት - መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት ይበርቃሉ/ብልጭ ይላሉ እንዲል።
የመብረቅ ተፈጥሮ እንደምን ነው ቢሉ? ውኃው በደመና አይበት ተቋጥሮ በነፋስ ወደል ጋዝ ተጭኖ ሲመጣ ደመናና ደመና በተጋጨ ጊዜ እንደ አረቄ ከውኃ ይወጣል ወተት ሲገፋ ቅቤ እንዲወጣው።
ነፋሳትን ከየሳጥናቸው የሚያወጣቸው እሱ ነው ለአሥራ ሁለቱ ነፋሳት አሥራ ሁለት መሳክው አሏቸው። በምሥራቅ ስድስት በምዕራብ ስድስት፤ ከዚህ እየመጠነ የሚያወጣቸው እሱ ነው። አንድ ጊዜ የወጡ እንደሆነ አንድም መጥኖ ባያወጣቸው ዓለምን የሚያሳልፉ ናቸውና።
488 views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 04:44:51

791 views01:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 04:39:41

722 views01:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 15:38:44 መዝሙር በቀዳሚ ገብረ ከሐምሌ ፲፯ እስከ ሐምሌ ፳፫

(በ፪/ዩ) በቀዳሚ ገብረ እግዚአብሔር ሰማየ ወምድረ ወኵሎ ፈጺሞ አዕረፈ በሰንበት ወይቤሎ ለኖኅ አመ አይኅ ግበር ታቦተ በዘትድኅን አነ አቀውም ኪዳንየ ዘምስሌከ ለዓለም ከመ ዳግመ ለምድር ኢያማስና በአይኅ ከመ አሀባ ለምድር ሣዕረ ሐመልማለ ክረምተ ወሐጋየ ዘርዐ ወማዕረረ ዝኬ ውእቱ ጸጋሁ ለእግዚአብሔር በአማን ኢይኄሱ ቃሎ ዘነበበ።
ትርጕም፦
በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ ሁሉን ፈጽሞ በሰንበት አረፈ በጥፋት ውኃ ጊዜ ኖኅን የምትድንበትን መርከብ ሥራ አለው እኔ ዳግመኛ ምድርን በጥፋት ውኃ እንዳላጠፋት ለዘለዓለም ኪዳኔን ከአንተ ጋር አቆማለሁ/አጸናለሁ ለምድር ሣርን ልምላሜን ክረምትን በጋን ዘርና መከርን እሰጣት ዘንድ ኪዳኔን ከአንተ ጋር አጸናለሁ የእግዚአብሔር ስጦታው ይህ ነው በእውነት የተናገረውን ቃሉን አይዋሽም።
የዕለቱ ምንባባት፦
ቲቶ ፫፥፩ - ፍ፤
፩ጴጥ ፬፥፮ - ፲፰፤
ግብ ፳፰፥፩ - ፲፯፤
ወንጌል፦ ማቴ ፳፬፥፴፮ - ፍጻሜ፤ ወይም ማር ፮፥፵፯ - ፍጻሜ፤
ቅዳሴ - ዘኤጲፋንዮስ
የዕለቱ ምስባክ፦
እስመ ትቤ ለዓለም አሐንጽ ምሕረተ፤
በሰማይ ጸንዐ ጽድቅከ፤
ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ። መዝ ፹፰፥፪
ትርጕም፦
ምሕረትን ለዘለዓለም አጸናለሁ ብለሃልና፤
ጽድቅህ በሰማይ ጸና፤
ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ።
ምሥጢር፦
አሐንጽ ያለውን እገብር ሲል ነው ቸርነትን ለዘለዓለም አደርጋለሁ ማለት አጸናለሁ ብለሃልና "አጽንዐ ምሕረቶ እግዚአብሔር ላዕለ እለ ይፈርህዎ - እግዚአብሔር በሚፈሩት ላይ ምሕረቱን አጸና" እንዲል መዝ ፻፪፥፲፩
ቸርነትህ እንደ ሰማይ ጸንቶ ይኖራል። ይህም በምድር ላይ የቱንም ያህል መናወጥ ቢደረግም ሰማይ እንደማይናወጥ የኃጢአታችን ብዛት በኖኅ ዘመን የገባልልንን ኪዳን እንዲናወጥ የማያደርገው መሆኑን መናገር ነው። በደመና የሚሳለው ምልክት እስካሁን አልተለወጠምና።
አንድም ቸርነትህ በፈጢረ ፀሐይ ጸና። በናቡከደነጾር ያሳይበታል "አነ ዘአሠርቅ ፀሐየ - ፀሐይን የማወጣ እኔ ነኝ” እስከ ማለት ደርሶ ነበርና
አንድም ሊቃነ መላእክትን ሠራዊተ መላእክትን በመፍጠር ጸና። "ገባሬ መላእክት አበ ኵሉ ዓለም - የመላእክት ፈጣሪ የዓለሙ ሁሉ አባት" እንዲል።
ትቤ ያለበት ነው ለአባትነት ከመረጥኋቸው ከወዳጆቼ ከባለሟሎቼ ከአብርሃም ከይስሐቅ ከያዕቆብ ጋር መሐላን ተማማልሁ ብለህ ነበር ማለት ይህንን መሐላ አስብ አስበህ ይቅር በለን ማለት ነው።
ወይም፦
ሐወፅካ ለምድር ወአርወይካ፤
ወአብዛኅኮ ለብዕላ፤
ፈለገ እግዚአብሔር ምሉዕ ማያተ። መዝ ፷፬፥፱
ትርጕም፦
ምድርን ጐበኘኻት አረካሃትም፤
ብልጥግናዋን እጅግ አበዛህ፤
የእግዚአብሔር ወንዝ ውኆችን የተመላ ነው።
ምሥጢር፦
ይህችን ዓለም በረድኤት ጐበኘሃት፤ ቦ ኢየሩሳሌምን ከሰባ ዘመን በኋላ ጐበኘሃት ማለት የዘሩባትን እንድታበቅል የተከሉባትን እንድታጸድቅ አደረግሃት።
የዚችን ዓለም ቦ የኢየሩሳሌምን ብዕለ ሥጋዋን ማለትም አዝርዕቱን አትክልቱን አበዛህላት፤ ቦ ለምእመን ብዙ ጸጋ ክብር የሚገኝበትን ልጅነትን ሰጠሃት።
እግዚአብሔር የፈጠራቸው አራቱ አፍላጋት ኤፌሶን ኤፍራጥስ ግዮን ጤግሮስ ውኃን የተመሉ ናቸው።
774 views12:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 05:05:32 https://docs.google.com/forms/d/1yeNCTJcuerriSX8d2ILtLL2yeCM2_d6cHhrzgdCxxQc/edit
702 views02:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 02:41:23
1.3K views23:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 00:48:35

1.4K views21:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ