Get Mystery Box with random crypto!

✞ ኤፍታህ በማለዳ

የቴሌግራም ቻናል አርማ eftah_bemaleda — ✞ ኤፍታህ በማለዳ
የቴሌግራም ቻናል አርማ eftah_bemaleda — ✞ ኤፍታህ በማለዳ
የሰርጥ አድራሻ: @eftah_bemaleda
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 654
የሰርጥ መግለጫ

📣ይህ ✞ ኤፍታህ በማለዳ የተባለው ኦርቶዶክሳዊ ዕውቀትን መማማሪያ እንዲሁም ስለሀይማኖታችን እንድናቅና "የሰው ጠላት የለኝም" በማለት ጠላታችን ዲያብሎስን በመቃወም ከክርስቶስ ጋር በመሆን ለበረከትና ለፀጋ በመትጋት መንግስትቱን ለመውረስ የምንማማርበት ነው። እግዚአብሔር ይርዳን።
በተከከታታይ የማንቂያ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን በኤፍታህ ይጠብቁን።
@Eftah_bemaleda

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-24 09:00:42
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሰን
በፍቅር ተስቦ የወረደው ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የፍቅሩን ፍፃሜ በመስቀል ላይ ገልፆልን ሀያል ጌታ በመሆኑ ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል ረድኤት በረከቱ በእያለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም ተነስቷል በዚህ የለም #መድኃኔዓለም

@Eftah_bemaleda
1.8K viewsedited  06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-22 12:06:22 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸዉ አምስቱ ችንካሮች (ሚስማሮች) ስም፦

#1ኛ ሳዶር
#2ኛ አላዶር
#3ኛ ዳናት
#4ኛ አዴራ
#5ኛ ሮዳስ

አምስቱ የእመቤታችን ኃዘናት፦

#1ኛ ከአምስቱ አንዱ አይሁድ እንዲገድሉክ በቤተ መቅደስ ስምዖን ትንቢት በተናገረ ጊዜ ነዉ።ሉቃ 2÷34
#2ኛ ሁለተኛዉም ሦስት ቀን በቤተ መቅደስ ባጣሁህ ጊዜ ነዉ።ሉቃ 2÷41
#3ኛ ሦስተኛዉም እጅህን እግርህን አስረዉ በጲላጦስ አደባባይ የገረፉህን ግርፋት ባሰብኩ ጊዜ ነዉ።ዮሐ19÷1
#4ኛ አራተኛዉም በዕለተ አርብ እራቆትህን ቸንክረዉ በሁለት ወንበዴዎች መካከል እንደሰቀልኩ ባሰብኩ ጊዜ ነዉ አለችዉ። ዮሐ19÷17
#5ኛ አምስተኛዉም ወደ ሐዲስ መቃብር ዉስጥ እንዳወረዱህ ባሰብኩ ጊዜ ነዉ።ዮሐ 19÷38

ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈፀሙ 7ቱ ተአምራት፦

#1ኛ ፀሐይ ጨልሟል
#2ኛ ጨረቃ ደም ሆነ
#3ኛ ከዋክብት እረገፉ
#4ኛ ዓለቶች ተሰነጠቁ
#5ኛ መቃብር ተከፈቱ
#6ኛ ሙታን ተነሱ
#7ኛ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ

ሰባቱ የመስቀል ላይ ንግግሮች፦

#1ኛ አምላኬ አምላኬ ለምን ተዉከኝ።ማቴ 27÷46
#2ኛ አባት ሆይ የሚያደርጉት አያዉቁምና ይቅር በላቸዉ።
ሉቃ 23÷34
#3ኛ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር እንድትኖር በእዉነት እነግረሃለሁ።
ሉቃ 23÷43
#4ኛ እነሆ ልጅሽ አነዃት እናትህ።ዮሐ 19÷26
#5ኛ ተጠማሁ።ዮሐ 19÷28
#6ኛ አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ።ሉቃ 23÷46
#7ኛ የተፃፈ ሁሉ ደረሰ ተፈፀመ አለ።ዮሐ19÷30

የአምላካችን ቸርነትና የእመቤታችን ምልጃ አይለየን አሜን ፫


@Eftah_bemaleda
871 views09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-22 12:01:49 " ሕማማት መስቀል" ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦

1. በብረት ሐብለ መጋፊያና መጋፊያው እስኪጋጠም ድረስ የኋሊት መታሰሩ
2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ
3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው
4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ
5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ
6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ
7. 6666 ጊዜ መገረፉ
8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ
9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ
10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀልበችንካር መቸንከሩ
11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ
12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ
13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።

@Eftah_bemaleda
1.1K views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-21 10:25:53 ሕማምህን ላስብ

ከእኔ ምን አይተህ ነው
እንዴት ብትወደኝ ነው
ግርፋቴን ወስደህ አንተ የተገረፍከው
ከኔ ምን አይተህ ነው
እንዴት ብትወዳኝ ነው
እኔ እንድናገር አንተ ግን ዝም ያልከው
እንዴት ብትወደኝ ነው

ማንስ ለጠላቱ ይህን ያህል ይደክማል
እራሱንስ ለሞት አሳልፎ ይሰጣል
ያንተ ግን ይለያል
ያንተ ግን ይደንቃል
ከርስት ልትመልሰኝ የህማም ሰው ሆነሀል
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር

በለሷ ለምልማ በቅጠል ብታምር
ፍሬ ግን የላትም ላንተ ሚሆን ነገር
አንተ ግን ስለኔ ብዙውን ሆነሀል
እርቃንህን ተሰቅለህ እኔን አልብሰሀል
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር

እንዳላየ አልፎኛል ሌዋዊውም ካህኑ
አለም እንደዚህ ናት ከጨለመ ቀኑ
በዘይት ጠገንከኝ በወይንህ አከምከኝ
በያሪኮ መንገድ ቆስየ ብታየኝ
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር

ፍቅርህ ይበረታል ፍቅርህ ይለውጣል
ያየሁት መዳፍህ ልቤን ቀስቅሶታል
ይህ ሁሉ ለእኔ ነው መከራ ህማሙ
እንደ አዲስ ፈጥሮኛል በከበረ ደሙ
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር

@Eftah_bemaleda
418 views07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 13:38:38
ሰሙነ ሕማማት

@Eftah_bemaleda
1.2K views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-08 17:29:05 ያለን #አንድ ነው፤ ነገር ግን ሁሉን መሆን ይችላል!! እርሱም፦ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

❝ጴጥሮስ ግን፦ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን #ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።❞
ሐዋርያት 3፥6

Join - @Eftah_bemaleda
852 views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 16:50:59
መጋቢት ፳፯ በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ! "ሊቃነ መላዕክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤ ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፤በመኳንንት በሚፈርደው በርሱ ፈረዱበት!"

Join - @Eftah_bemaleda
1.4K views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 16:09:36 ማን ያምናል አሁን የእኛን መዳን
በአለም እርኩሰት ለሚያውቀን
እንዲሁ ነጻ ናችሁ ያልከን
ተባረክ ፈቅደህ የባረከን
ኑሮአችን ነበር የጨለማ
ምንቀኝ የአልምን ዜማ
ሳንጠፋ ሳንገባ ከጥልቁ
ተማርን ታይቶልን ሰንደቁ

Join - @Eftah_bemaleda
864 views13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 08:45:44 ምህረቱ ለዘላለም ነውና
ቸርነቱ ለዘላለም ነውና
እግዚአብሔርን አመሰግኑ

ከመከራ ዘመን መራመጃ ሆኖ
ልጆቹን ያወጣ በግርማው ሸፍኖ
ይጋር ሰሀዶታ የጸጥታ ወደብ
ወደ ተጨቆኑት በፍትህ የሚቀርብ
የእስራኤልን ቅዱስ አመስግኑ
መልካሙን እረኛ አመስግኑ
ለድሆች የሚፈርድ አመስግኑ
እውነተኛ ዳኛ አመስግኑ

@Eftah_bemaleda
1.3K views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-19 14:27:00 “…እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ፥ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተም ታዝናላችሁ፥ ነገር ግን ኀዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል። ሴት በምትወልድበት ጊዜ ወራትዋ ስለ ደረሰ ታዝናለች፤ ነገር ግን ሕፃን ከወለደች በኋላ፥ ሰው በዓለም ተወልዶአልና ስለ ደስታዋ መከራዋን ኋላ አታስበውም። እንግዲህ እናንተ ደግሞ አሁን ታዝናላችሁ፤ ነገር ግን እንደ ገና አያችኋለሁ ልባችሁም ደስ ይለዋል፥ ደስታችሁንም የሚወስድባችሁ የለም።”
ዮሐ 16፥ 20-23

@Eftah_bemaleda
1.2K views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ