የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመዝጊያ እና የውድድር ዓመቱ ምርጦች ሽልማት ስነ ስርአት ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል ሲካሄድ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ለተመረጠው ጋቶች ፓኖም የተዘጋጀውን ሽልማት አበርክተዋል። ጋቶች ፓኖም በኮከብ ተጫዋችነት ፣ አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ በኮከብ አሰልጣኝነት ፣ ቻርለስ ሉክዋጎ በኮከብ ግብ ጠባቂነት ፣ አላዛር ማርቆስ በምርጥ ወጣት ተጫዋችነት ፣ ይገዙ ቦጋለ በከፍተኛ ጎል አግቢነት ፣ ኢ/ል ዳኛ ኃይለየሱስ ባዘዘው በምስጉን ዋና ዳኝነት ፣ ኢ/ል ረዳት ዳኛ ትግል ግዛው በምስጉን ረዳት ዳኝነት ኮከብ ሆነው የተሸለሙ ናቸው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአክሲዮን ማህበሩ ዓመቱን በደማቅ ሁኔታ በማጠናቀቁ እንዲሁም በኮከብነት ለተሸለሙት በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ሲል ልባዊ ደስታውን ይገልፃል። 524 viewsedited 18:23