በህገ-ወጥ መንገድ የተገጠሙ ቆጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በአዲስ አበባ ከተማ ገርጂ ጎሮ አካባቢ ልዩ ስሙ አሳማ እርባታ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አስራ ሰባት ቆጣሪዎች በህገ-ወጥ መንገድ ተገጥመው ተገኝተዋል፡፡
በህገ-ወጥ መንገድ ተገጥመው የተገኙት ቆጣሪዎች ከነፍጆታቸው አጠቃላይ ግምት ከሶስት መቶ አርባ ሶስት ሺ ብር በላይ ነው፡፡
የምስራቅ አዲስ አበባ ዲስትሪክት ህግ ክፍል ከፖሊስ ጋር በመተባበር በህገ-ወጥ መንገድ የተገጠሙትን ቆጣሪዎች፣ኬብልና ምሰሶ ተነስቶ ወደ ተቋሙ ገቢ እንዲሆን አድርጓል፡፡
የአካባቢው ፖሊስ ህገ-ወጥ ተግባሩ ላይ ምርመራ እያከናወነ ይገኛል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et