ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድምቀት ተከበረ የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ አገልግሎት ዛሬ የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም በሃገር አቀፍ ደረጃ ለ47ኛ ጊዜ የሚከበረውን አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8 በድምቀት አክብሯል፡፡ ክብረ በዓሉ የተከበረው “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ቃል ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላን ጨምሮ የሰራተኛ ማህበር ሊቀ መንበር፣ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣ ሰራተኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው ዕንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በዕለቱ የተሻለ አፈጻፀም ያስመዘገቡ ሴት ሰራተኞች የዕውቅና የሰርተፍኬት እና የማበረታቻሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ ይጎብኙ፡- http://www.eeu.gov.et 2.0K views15:27