Get Mystery Box with random crypto!

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትናንትናዉ እለት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አደጋ የደረሰባቸዉ | Educate Ethiopia

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትናንትናዉ እለት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ አደጋ የደረሰባቸዉን ተማሪዎች ጠየቁ
---------------------------------------------------------------------

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትናንትናዉ ዕለት አደጋ የደረሰባቸዉን በሃዋሳ ዩኒቨርስቲ የሚፈተኑ የ2014 ዓም 12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደህንነት ለመጠየቅ ዛሬ ጠዋት ሀዋሳ ሪፌራል ሆስፒታል ተገኝተዋል፡፡

“አሁን ዋናዉ የእናንተ ማገገም ነዉ፡፡ ለፈተናዉ አትጨነቁ” በማለትም የተጎዱ ተማሪዎች በጤንነታቸዉ ዙሪያ እንዲያተኩሩ መክረዋል፡፡

በትናንትናዉ እለት ህይወቱ ላለፈዉ ተማሪም የተሰማቸዉን ከፍተኛ ሀዘን ገልጸዉ ለተማሪዉ ወላጆች እና ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

በደረሰዉ ጉዳት እንደአገር እናዝናለን፡፡ ነገር ግን ሂደቱ የፈተና ስርዓቱ ከስርቆት ተጠብቆ ተማሪዎች በራሳቸዉ ጥረት ዉጤታማ እንዲሆኑ እና የተሻለች አገር የመገንባት በመሆኑ በዚህ ተስፋ መቁረጥ የለብንም ብለዋል፡፡ ወላጆችም ይህንን ተረድተዉ ከትምህርት ማህበረሰቡ ጋር በጋራ እንዲቆሙ ጠይቀዋል፡፡

የተከሰተዉ የድልድይ መደርመስ አደጋ ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር ተማሪዎቹን ለማዳን ለተረባረቡ የጤና ተቋማት ፣ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ እና የአካባቢዉ ነዋሪዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ትናንት በደረሰዉ አደጋ ምክንያት ተቋርጦ የነበረዉ ፈተና ዛሬ የተጀመረ ሲሆን ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የፈተና አሰጣጡንም ጎብኚተዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር !