#EthioTelecom #SafaricomEthiopia
ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሰረተ ልማት መጋራት እና ትስስር ላይ ያደጉት ዘርፈ ብዙ ድርድሮች በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገልጿል።
በቅርቡ በኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም መካከል ስምምነት ይፈረማል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኢትዮ ቴሌኮም የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በሌላ በኩል ፥ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሚያዚያ 1 /2014 አገልግሎት ለመጀመር እቅድ እንደነበረው ከዚህ በፊት መግለፁ ይታወሳል፤ ነገር ግን በተባለው ቀን አገልግሎት ያልጀመረ ሲሆን በቅርቡ አገልግሎት እንደሚጀምር ይጠበቃል።
@EBS_TV_NEWS