Get Mystery Box with random crypto!

#Afar ' በእሳት አደጋው 160 የሚጠጉ ሱቆች እና የመኖሪያ ቤቶች ወድመዋል። በሰው ላይ የደረ | EBS TV NEWS

#Afar

" በእሳት አደጋው 160 የሚጠጉ ሱቆች እና የመኖሪያ ቤቶች ወድመዋል። በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም " - ሰሙሮቢ ገልዐሊ ወረዳ

በአፋር ክልል ሰሙሮቢ ገልዐሊ ወረዳ በድንገት በተከሰተ የእሳት ቃጠሎ በግምት ከ160 በላይ የሚጠጉ ሱቆች እና መኖሪያ ቤቶች መውደማቸውን የወረዳው አስተዳድር አሳውቋል።

የሰሙሮቢ ገልዐሊ ወረዳ አስተዳድር አቶ ሀሰን ሀንዲ ለአፋር ብዙሀን መገናኛ በሰጡት ቃል ፤ " የእሳት ቃጠሎ አደጋው የደረሰው ወደ 10 : 00 ሰዓት አካባቢ በድንገት ከቢንዝል መሸጫ ቤት በተነሳ እሳት ነው " ብለዋል።

በድንገተኛው የእሳት አደጋ ምክንያት የደረሰው ውድመት ወደፊት የሚጣራ ሁኖ በግምት ግን ከ80 በላይ መኖሪያ ቤቶች እንደዚሁም ወደ 80 ሊጠጋ የሚችል የተለያዩ የንግድ ሱቆች ወድመዋል።

በእሳት አደጋው በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ አሳውቀዋል።

በአካባቢው ላይ ከፍተኛ ንፋስ መኖሩ እና የውሀ እጥረት በመኖሩ ቃጦሎው በፍጥነት በመባባሱ ምክንያትም እሳቱን ለመቆጣጠር ባለመቻሉ ከፍተኛ ውድመት መከሰቱን አስተዳዳሪው አስረድተዋል።

ለተጎጂዎቹ አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደረግም ጥሪ አቅርበዋል።

በብዛት የቢንዚል ሽያጭ ከሚከናወንበት ቦታም በቀላሉ የእሳት አደጋ እየተፈጠረ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቂ ሊደረግ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

መረጃው የአፋር ብዙሀን መገናኛ ድርጅት ነው።

@EBS_TV_NEWS