2022-05-26 23:36:17
ሕዝቅኤል 22 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ የእግዚአብሔርም ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤
²⁴ “የሰው ልጅ ሆይ፤ ምድሪቱን፣ ‘አንቺ ያልነጻሽ በቍጣም ቀን ዝናብ ያላገኘሽ ምድር ነሽ’ በላት።
²⁵ መሳፍንቷ እያገሣ ግዳዩን እንደሚቦጫጭቅ አንበሳ በውስጧ ያሤራሉ፤ ሕዝቡን ይበላሉ፤ ንብረትንና የከበሩ ነገሮችን ይነጥቃሉ፤ ብዙዎችንም ሴቶች መበለት ያደርጋሉ።
²⁶ ካህናቷ በሕጌ ላይ ያምፃሉ፤ ንዋያተ ቅድሳቴን ያረክሳሉ፤ የተቀደሰውን ከረከሰው አይለዩም፤ በጐደፈውና በንጹሑ መካከል ልዩነት እንደሌለ ያስተምራሉ፤ ሰንበታቴን ከማክበር ዘወር ብለዋል፤ በዚህም በመካከላቸው ተንቄአለሁ።
²⁷ በውስጧ የሚገኙ መኳንንቷ ግዳይ እንደሚቦጫጭቁ ተኵላዎች ናቸው፤ በግፍ ትርፍ ለመሰብሰብ ደም ያፈሳሉ፤ ሕይወትም ያጠፋሉ።
²⁸ ነቢያቷም በሐሰት ራእይና በውሸት ሟርት ይህን ሁሉ ድርጊት ያድበሰብሱላቸዋል፤ እግዚአብሔርም ሳይናገር፣ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል’ ይላሉ።
²⁹ በምድሪቱ የሚኖረው ሕዝብ ይቀማል፤ ይዘርፋል፤ ፍትሕ በማጒደልም ድኻውንና ችግረኛውን ይጨቍናል፤ መጻተኛውንም ይበድላል።
³⁰ “ምድሪቱን እንዳላጠፋት ቅጥሩን የሚጠግን፣ በፈረሰውም በኩል በፊቴ የሚቆምላት ሰው ከመካከላቸው ፈለግሁ፤ ነገር ግን አንድም አላገኘሁም።
³¹ ስለዚህ መዓቴን አፈስባቸዋለሁ፤ በጽኑ ቍጣዬም አነዳቸዋለሁ፤ ያደረጉትንም በራሳቸው ላይ እመልሳለሁ፤ ይላል ጌታ እግዚአብሔር”።
፥አይጠፋም ከህኑም ማለዳ ማለዳ እንጨት ያቃጥልበታል፤የሚቃጠለውንም መሥዋዕት በዚያ ላይ ይረበርባል፥በዚያም የደኀንነትን መሥዋዕት ስብ ያቃጥላል ።"""
ትንሽዋ እሳት ብዙ ጨካ እንደምታቀጥል የመንፈሳዊ እሳት በዝች ምድር ላይ እንለኩስ።
Join us
Join us
@Divineservice1040
@Divineservice1040
@Divineservice1040
282 views𝕜𝕙𝕖𝕧𝕣𝕒 𝔸𝕓𝕚𝕟𝕖𝕥, edited 20:36