2022-08-25 15:35:06
በወጣቶች_አሰደናቂ ዋሻ ተፈለፈለ!
.............................................
#በመተሐራ_ቅዱስ_ሚካኤል_በወጣቶች_ሲፈለፈል_የነበረው_አስደናቂ_ዋሻ_ተጠናቀቀ
.........................
የምስራቹን ለሌሎች #Share በማድረግ አድርሱ!
#ይህ_ከታች_በፎቶ የምትመለከቱት በመተሐራ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ህንጻ ቤተመቅደስ ፊት ለፊት የሚገኘው በብርቱዎቹ የናታኔም ወጣቶች ተሰርቶ የተጠናቀቀው እጅግ አስደናቂ ዋሻ ነው። ጥቂት ክፍተት ያለው ዋሻ አስቀድሞ በደብሩ ግቢ ውስጥ ነበር።
ይህንንም በልዩ ልዩ ጊዜ የነበሩና ወደ ስፍራው የመጡ ታላላቅ አባቶች በዋሻው የእጣን መዓዛ አልፎ አልፎም ብርሃን ይታያል በማለት ምስክርነታቸውን ይሰጡ ነበር።
የከተማው ኦርቶዶክሳዊም ይህን ዋሻ በተመለከተ ቁጥር በቁጭት እንደሌሎች ገዳማት ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው መቼ ነው ? በማለት በቁጭት ይናገር ነበር።
ነገር ግን ከባድና ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ በመሆኑ ተሰርቶ የጸሎት ቤት፣ለሱባኤ መዝጊያ ሆኖ ለማየት ለዘመናት ከጉጉት ያለፈ አልነበረም። ገናናው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ስራውን የሚሰራበት ዘመኑ ደረሰና የመተሐራ ቅዱስ ሚካኤል ናታኔም የምንጣፍ ማህበር ልጆቹን አስነስቶ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ሙሉ ለሙሉ ዓለት የሆነው የዋሻ ክፍል ከፍተኛ የሆነውን ሙቀት ታግዞ በላብ እየታጠበ ከፍተኛ ተጋድሎ በመፈጸም ያለማቋረጥ በመዶሻ እየፈረከሰ፣በዶማ እየናደ በአካፋ እየዛቀ እሳት በሚተፋ ዋሻ ውስጥ በከፍተኛ ትጋት በድንጋይ ስለት እግራቸው እየተቆረጠ በመዶሻ እጃቸው እየተቀጠቀጠ በከፍተኛ የደስታ ስሜት ተጋድሎ በመፈጸም የዋሻውን ስራ ሙሉ ለሙሉ ከፍጻሜው አድርሰውታል።
አሁን እንደምትመለከቱት በጣም ሰፊ የሆነ ቁመቱም በጣም ከፍ ስላለ ቀዝቃዛ የሆነ ለጸሎትና ለሱባኤ ምቹ የሆነ ዋሻን ጠርበው አጠናቀዋል። በማህበሩ አባል በሆነች በወጣት እርብቃ የተሳሉ የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ቅዱሳን ስዕላትም ተለጥፈው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል።እነዚህ ብርቅዬ የመተሐራ የተዋህዶ ልጆች ሙሉ አባላቱ የግል ስራቸውን ጭምር በመተው ለዚህ ታላቅና አስደናቂ ተግባር ዋጋ ከፍለዋል። በእውነት በዚህ ዘመን #ድንጋይ_ፈልጦ_ዋሻ የሚገነባ ያውም በከተማ ከማየት በላይ ምን የሚያስደስት ነገር አለ ?ምንም።
ደግሞም እነዚህ ልጆች ሁሌም መከባበራቸው ፣መዋደዳቸውና ለአገልግሎት ያለቸው ትጋትና ብርታት በሚሰሩት በጎ ተግባር ከከተማው አልፈው በመላው ገዳማትና አድባራት የደብራቸውን ስም በወርቅ ቀለም እያጻፉ ነው።የእነርሱን ደግሞ በመንግሥተ ሰማያት!።
እቅዳቸው ተሳክቶ ዋሻውም ከፍጻሜ ደርሶ በብጹዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝ/ሐ/ብ/ቅ/ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ተመርቆ አገልግሎት ሊጀምር ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል።አምላክ ለምርቃቱ ቀን ለመድረስ ይፍቀድልን።
#የመተሐራ_ቅዱስ_ሚካኤል_ናታኔም_ማህበር_ወጣቶች የአግልግሎት ዘመናቸው በቤቱ ይለቅ።ቅዱስ ሚካኤል ጥላ ከለላ ጋሻ መከታ ሆኖ ፍጻሚያችሁን ያሳምርላችሁ።
ይህንን ያደረገ የቅዱስ ሚካኤል አምላክ የተመሰገነ ይሁን
መምህር ኤፍሬም ሀብተ ማርያም
ለተለያዩ መረጃዎች ፔጁን #Like ያድርጉ!
ቴሌግራም t.me/DebteraMedia
1.5K views12:35