Get Mystery Box with random crypto!

Debtera Media

የቴሌግራም ቻናል አርማ debteramedia — Debtera Media D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debteramedia — Debtera Media
የሰርጥ አድራሻ: @debteramedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.18K
የሰርጥ መግለጫ

ደብተራ ሚዲያ የእውነት ድምጽ!
ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!👇
በዩቲዩብ 👉 https://bit.ly/3bMfT8D
በፌስቡክ 👉 fb.me/DebteraMedia

በቴሌግራም 👉 t.me/DebteraMedia
ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ሆነ መረጃ በ t.me/DebteraMedia_Bot ማድረስ ትችላላችሁ።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 22:34:31
የዓለማችን አራት_ህጻናት
1 በሶሪያ ጦርነት የቆሰለው ህፃን ለዶክተሩ «እኔ ወደ ፈጣሪ መሄዴ ነው የሆነውን ሁሉ እነግረዋለው»•••
2 ኢራቅ ሞሱል ውስጥ ቆስላ እየሮጠች ካሜራ ማኑ ሲቀርፃት «አጎቴ እባክህ ቪዲዮ አትቅረጸኝ ምክንያቱም ሂጃብ አለበስኩም»•••
3 አንድ ህፃን በፍልስጤም እጅግ በጣም ይራብና «ፈጣሪ ሆይ እባክህ በቶሎ ውሰደኝ አንተ ከወሰድከኝ በገነት ውስጥ አልራብም እዛ እበላለሁ»•••
4 በአፍጋኒስታን ጦርነት እጁ ክፉኛ የቆሰለው ህፃን ለሕክምና ዶክተር ጋ ወስደውት ለዶክተሩ «ዶ/ር እጄን ስትቆርጠው ልብሴን አትቁረጠው ተጠንቀቅ ምክንያቱም እኔ ሌላ ልብስ የለኝም እና» አለው•••
የጦርነት አስከፊነትን እንማር
ሠላም ለሀገራችን

#ሸር!

@DebteraMedia
1.1K views19:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:31:25
ዋግ ኽምራ የጦር ውሎ…!!

"…ንጋት 12:00 ሰዓት ጀምሮ ህወሓት ወደ ዋግ ኽምራ ሰቆጣ ለመግባት ከሰቆጣ ፋጥዝጊ ከሚባል ተራራ ላይ ሁና ወደ ዝቋላ ወረዳ ቀዳሚት ቀበሌ ከባድ መድፍ በመተኮስ የተለመደ ትንኮሳዋን ትጀምራለች። ነገር ግን እንደ ቆቦው ግንባር በርግጎ የሚሸሽ፣ የሚፈረጥጥ፣ የማይናበብ የኢትዮጵያ ሠራዊት በዚህኛው ግንባር አልገጠማትም። እንዲያውም አጸፋውን አከበዱባት።

"…በውጊያው ያ ድሮ ኢትዮጵያ በምታውቀው፣ መሸነፍ፣ መበርገግ፣ መሮጥ በማያውቀው ጀግና ስንለው በኩራት ደረታችንን ነፍተን በምንመሰክርለት በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዎትና ጀግኖቹ በዐማራ ልዩ ኃይል፣ በዐማራ ፋኖ እና በዐማራ ሚኒሻዎች ጽኑ ተጋድሎ ህወሓትን በመመከት እስከ ቀኑ 10 ሰዓት ድረስ ውጊያው መቆየቱም ተነግሯል። ከ10ሰአት በኋላ ግን በሰቆጣ የከባድ መሣሪያ ድምፅ አልተሰማም።

"…ህወሓት በ3 አቅጣጫዎች ነበር መድፍ ስትተኩስ የዋለችው። 1ኛ ወደ ዝቋላ ቀዳሚት ቀበሌ። 2ኛ አበርገሌ ወረዳ፣ 3ኛ ፃግብጂ ወረዳ። የፃግብጅ ድልድዩን ሰብረውት የነበረ ቢሆንም ያ ድሮ የምናውቀው መመኪያችን የምንለው፣ የሃገር ኩራት የሃገር መከላከያ ሰራዊታችን ጊዜያዊ ድልድይ በአስቸኳይ በመሥራት ጥራሪን ተሻግሮ ወደ ኮረም መስመርም አልፏል። ገስግሷልም።

"…ጥምር ጦሩ ማታ አበርገሌ ጠዋት መቀሌ ነው የምገኘው እያለ ሲሆን ወደ ኮረም ከገሰገሰና ኮረም ከገባ ግን ወልድያን እይዛለሁ ብሎ በወጥመድ ውስጥ የተቀረቀረው የህወሓት ሰራዊት የመማረክ ዕድል ካልገጠመው በቀር ለወሬ ነጋሪም መትረፉን እንጃ ነው የሚሉት የመረጃ ምንጮቼ። በአፋር በኩል ደግሞ መቀሌ 50 ኪሎሜትር ነው የሚርቀው።

"…ይህ የእኔ የዘመዴ መረጃ ነው።

• ድል ለኢትዮጵያ ሠራዊት…!!
• ለዐማራ ልዩ ኃይል…!!
• ድል ለዐማራ ፋኖ…!!

@ዘመዴ

@DebteraMedia
861 views19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:19:44

848 views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 15:33:45

925 views12:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 13:02:11
#ክቡራን_ዶክተሮች!

ብጹዕ ዶክተር አቡነ ኤርሚያስ የሰሜን ወሎ እና የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል።
እና ክብርት ዶክተር ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እንኳን አደረሳችሁ ደስ ብሎናል።
ብጹዕ አባታችን ከዶክትሬቱ በላይ ሰማያዊ ማዕረግ የሆነውን ብጹዕ መባሉ ክምንም ይበልጣል ቢሆንም ለምድራዊው ስራዎ ሲያንስዎት እንጅ አይበዛብዎትም!

በቴሌግራም t.me/DebteraMedia
1.3K views10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 10:09:46 Watch "የክብር ዶክትሬት አሰጣት ስነ ስርዓት ከባሕርዳር ዩኒቨርስቲ!" on YouTube


1.2K views07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 15:37:32
1.6K views12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 15:35:06 በወጣቶች_አሰደናቂ ዋሻ ተፈለፈለ!
.............................................
#በመተሐራ_ቅዱስ_ሚካኤል_በወጣቶች_ሲፈለፈል_የነበረው_አስደናቂ_ዋሻ_ተጠናቀቀ
.........................
የምስራቹን ለሌሎች #Share በማድረግ አድርሱ!

#ይህ_ከታች_በፎቶ የምትመለከቱት በመተሐራ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ህንጻ ቤተመቅደስ ፊት ለፊት የሚገኘው በብርቱዎቹ የናታኔም ወጣቶች ተሰርቶ የተጠናቀቀው እጅግ አስደናቂ ዋሻ ነው። ጥቂት ክፍተት ያለው ዋሻ አስቀድሞ በደብሩ ግቢ ውስጥ ነበር።

ይህንንም በልዩ ልዩ ጊዜ የነበሩና ወደ ስፍራው የመጡ ታላላቅ አባቶች በዋሻው የእጣን መዓዛ አልፎ አልፎም ብርሃን ይታያል በማለት ምስክርነታቸውን ይሰጡ ነበር።

የከተማው ኦርቶዶክሳዊም ይህን ዋሻ በተመለከተ ቁጥር በቁጭት እንደሌሎች ገዳማት ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው መቼ ነው ? በማለት በቁጭት ይናገር ነበር።

ነገር ግን ከባድና ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ በመሆኑ ተሰርቶ የጸሎት ቤት፣ለሱባኤ መዝጊያ ሆኖ ለማየት ለዘመናት ከጉጉት ያለፈ አልነበረም። ገናናው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ስራውን የሚሰራበት ዘመኑ ደረሰና የመተሐራ ቅዱስ ሚካኤል ናታኔም የምንጣፍ ማህበር ልጆቹን አስነስቶ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ሙሉ ለሙሉ ዓለት የሆነው የዋሻ ክፍል ከፍተኛ የሆነውን ሙቀት ታግዞ በላብ እየታጠበ ከፍተኛ ተጋድሎ በመፈጸም ያለማቋረጥ በመዶሻ እየፈረከሰ፣በዶማ እየናደ በአካፋ እየዛቀ እሳት በሚተፋ ዋሻ ውስጥ በከፍተኛ ትጋት በድንጋይ ስለት እግራቸው እየተቆረጠ በመዶሻ እጃቸው እየተቀጠቀጠ በከፍተኛ የደስታ ስሜት ተጋድሎ በመፈጸም የዋሻውን ስራ ሙሉ ለሙሉ ከፍጻሜው አድርሰውታል።

አሁን እንደምትመለከቱት በጣም ሰፊ የሆነ ቁመቱም በጣም ከፍ ስላለ ቀዝቃዛ የሆነ ለጸሎትና ለሱባኤ ምቹ የሆነ ዋሻን ጠርበው አጠናቀዋል። በማህበሩ አባል በሆነች በወጣት እርብቃ የተሳሉ የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ቅዱሳን ስዕላትም ተለጥፈው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል።እነዚህ ብርቅዬ የመተሐራ የተዋህዶ ልጆች ሙሉ አባላቱ የግል ስራቸውን ጭምር በመተው ለዚህ ታላቅና አስደናቂ ተግባር ዋጋ ከፍለዋል። በእውነት በዚህ ዘመን #ድንጋይ_ፈልጦ_ዋሻ የሚገነባ ያውም በከተማ ከማየት በላይ ምን የሚያስደስት ነገር አለ ?ምንም።
ደግሞም እነዚህ ልጆች ሁሌም መከባበራቸው ፣መዋደዳቸውና ለአገልግሎት ያለቸው ትጋትና ብርታት በሚሰሩት በጎ ተግባር ከከተማው አልፈው በመላው ገዳማትና አድባራት የደብራቸውን ስም በወርቅ ቀለም እያጻፉ ነው።የእነርሱን ደግሞ በመንግሥተ ሰማያት!።

እቅዳቸው ተሳክቶ ዋሻውም ከፍጻሜ ደርሶ በብጹዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝ/ሐ/ብ/ቅ/ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ተመርቆ አገልግሎት ሊጀምር ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል።አምላክ ለምርቃቱ ቀን ለመድረስ ይፍቀድልን።

#የመተሐራ_ቅዱስ_ሚካኤል_ናታኔም_ማህበር_ወጣቶች የአግልግሎት ዘመናቸው በቤቱ ይለቅ።ቅዱስ ሚካኤል ጥላ ከለላ ጋሻ መከታ ሆኖ ፍጻሚያችሁን ያሳምርላችሁ።

ይህንን ያደረገ የቅዱስ ሚካኤል አምላክ የተመሰገነ ይሁን

መምህር ኤፍሬም ሀብተ ማርያም

ለተለያዩ መረጃዎች ፔጁን #Like ያድርጉ!

ቴሌግራም t.me/DebteraMedia
1.5K views12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 20:23:29
1.3K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 20:23:23 ማሳሰቢያ በአርቲስት መቅደስ ፀጋዬ

የኔ ታዋቂነትም ሆነ እንዳላችሁኝ የእውቀት ደረጃ የአምላኬን እናት በአደባባይ እንዳላወድሳት የሚያደርገኝ ከሆነ #ጥንቅር_ብሎ_ይቅር!! ቁርጥ መልሴ ነው። እውነት ነው መቅደስ ፀጋዬ
==============================
ይህ የእኔ የግል ገፄ ሲሆን የኔን የግል አመለካከቶቼን እና እምነቶቼን የማንፀባርቅበት ነው። ሃይማኖቴ ደግሞ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መሆኑ ይታወቃል። ኦርቶክሳዊነቴን እናትና አባቴ ስላወረሱኝ ብቻ ሳይሆን አውቄው፣ ተረድቼው ትክክለኛነቱን አምኜ አምላኬን የማመልክበት ሃይማኖቴ ነው።

ትናንት የለጠፍኩትን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ተከትሎ የመጡልኝን አንዳንድ የሌላ እምነት ተከታዮች አስተያየቶችን ንቄ ለመተው ብሞክርም በግል ስልኬ እየደወሉ ቅድስት ድንግል ማርያምን የማወድስበት መንገድ ከኔ እንደማይጠበቅ መንገር እና ስለ አምላኬ ለኔ ለመስበክ መሞከርን ግን #ከንቀት_ቆጥሬዋለሁ።

እናም ይህ ሁኔታ ስለተደጋገመብኝ ነው አቋሜን ለመግለፅ አደባባይ መውጣት የፈለግኩት።

የኔ ታዋቂነትም ሆነ እንዳላችሁኝ የእውቀት ደረጃ የአምላኬን እናት በአደባባይ እንዳላወድሳት የሚያደርገኝ ከሆነ #ጥንቅር_ብሎ_ይቅር!! ቁርጥ መልሴ ነው። እናቴን ገና መቼ አመሰገንኳትና! መቼ ገና አወደስኳት!.....በእኔ በኃጢያተኛዋ እና በደካማዋ ሴት የሷ ስም ሲጠራ ክብሩ ለኔ ነው!! አምላኬ በምህረቱ ባይጎበኝ እመአምላክ ባታማልደኝ የአምላኬ ማደሪያ የሆነችውን የእናቴን ስም የመጥራት አቅሙስ ባልኖረኝ ነበር! እና እስትንፋሴ እስካለች #ቅድስት_ድንግል_ማርያምን እናቴን አወድሳታለሁ!! ስለ ማርያም አማላጅነት እመስክራለሁ!!

እግዚአብሔር ይመስገን በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በሙሉ የአምላክነት ክብሩ አለ። ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ፣ በማህሌቷ በመዝሙሯ አምልኮ የምታደርገው ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። እናም የ80 ቀን ልጅ እያለሁ በጥምቀት የተቀበልኩትና የማውቀው የማመልከውን አምላክ እያለኝ ጌታን ተቀበይ ብሎ ሙግት ለኔ አላዋቂነት ነው!!

የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆናቹ እጅግ የምወዳችሁ እና የማከብራቸው ጓደኞቼ እንዲሁም ቤተሰቦቼ አብረን በቆየንባቸው አመታት አንድም ቀን ስለእምነት ልዩነት ሳታነሱ አብሮነታችን ፀንቶ እንዲቆይ ስላደረጋችሁ ሳላመሰግናቹ አላልፍም። ለናንተ ያለኝ ፍቅር ብቻ ነው ተባረኩልኝ

በስተመጨረሻም ሀገር በከፋ ችግር ላይ ባለችበት በአሁኑ ወቅት እንደህዝብ አንድነታችንን አጠናክረን በየእምነት ተቋማችን አምላካችን ለሀገራችን ምህረቱን እንዲያመጣ እየከፋፈለን፣ እያጠፋን ካለው መንፈስ እንዲያላቅቀን መፀለይ እንጂ አንዱ የአንዱን ሃይማኖት በማንቋሸሽ ምዕመን ምልመላ ላይ መሯሯጥ አያዋጣንም።

ቸር እንሰንብት ወዳጆቼ!!

#LikeAndShare

@DebteraMedia
1.3K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ