2023-06-08 22:09:11
ማስታወቂያ
ለክፍል GC ኮሚቴ ተወካዮች በሙሉ:-
ለ ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ:-
1. ስለ #ባይንደር እና #መጽሔት
የ GC ኮሚቴ ባይንደር እና መጽሔት ለማሰራት የገበያ ጥናት ሲያካህድ ቆይቷል። ሆኖም ግን ጨረታ ለማውጣት የግድ ማሰራት የሚፈልጉ ተማሪዎች ብዛት መታወቅ ስላለበት ጨረታ ሳያወጣ ቀርቷል። ማለትም ድርጅቶች ለብዙ ተማሪዎች ባሰራን ቁጥር የዋጋ ቅናሽ የሚያደርጉ ሲሆን፣ የተማሪ ቁጥር ካነሰ ግን ዋጋ ይጨምራል።
ባደረግነው የገበያ ጥናት #ከፍተኛው_ዋጋ_እንደሚከተለው_ነው:-
1. #ባይንደር - 350 ብር
2. #መጽሔት - 1500 ብር
ይህን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ማሰራት የምትፈልጉ ተማሪዎች እስከ እሁድ ምሽት 11:30 ድረስ ብቻ የክፍል GC ተወካዮቻችሁ ጋር ወይንም Representatives ጋር እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
:- የክፍል GC ተወካዮች ወይንም Representatives ማሰራት የሚፈልጉ ተማሪዎችን ዝርዝር በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት እንድታሳውቁን በድጋሚ እናሳስባለን።
#ማሳሰቢያ
#@ #ከላይ_የተጠቀሰው_የብር_መጠን_ከፍተኛው_Maximum_ግምት_ሲሆን_ብዙ_ተማሪዎች_ባሰሩ_ቁጥር_የሚቀንስ_ይሆናል።
2. ስለ GC ካፕ
የ GC ካፕ ቅዳሜ ይጀምራል።
በተጨማሪም የቡድን ድልድል ዕጣ መውጣቱ ይታወቃል። 21 ዲፓርትመንቶች በዕጣው የተካተቱ ሲሆን ፣ Information Technology ዲፓርትመንት የሚጠበቅባቸውን መረጃ አሟልተው ለመወዳደር ቢመዘገቡም፣ #በስህተት በዕጣው ሳይካተቱ ቀርቷል። የ GC ኮሚቴውም ቅሬታቸው ትክክል እና አግባብ መሆኑን ስላመነበት ምድብ 11 ላይ በዕጣ ካለፈው ከ #Surveying ት/ት ክፍል ጋር እንዲጫወቱ ወስኗል።
የምድብ ድልድሉ ከታች ተያይዟል።
3. ስለ Defence
ብዙ ኮሌጆች ያለብንን ተደራራቢ ጫና በመገንዘብ #Defence እንዲቀር ማድረጋቸው ይታወቃል። ሆኖም ግን አንድአንድ ኮሌጆች ያላስቀሩ መሆኑን ለማወቅ ችለናል። ዲፈንስ ያልቀረላችሁ ኮሌጆች ሪፖርት እንድታደርጉልን እንጠይቃለን።
4. ስለ CostSharing
Costsharingን አስመልክቶ ብዙ ጥያቄ እየተነሳ መሆኑ ይታወቃል። ኮሚቴው በዚህ ጉዳይ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ መረጃ በማሰባሰብ እና ከሚመለከተው አካል ጋር በመወያየት ላይ ስለሚገኝ በትዕግስት እንድትጠብቁን እናሳስባለን።
@ጥያቄ፣ አስተያየት ወይም ሀሳብ ካሎት ለመቀበል ዝግጁ ነን።
የ GC ኮሚቴ
ሰኔ 1- 2015 ዓ. ም
@dbu11
@dbu_entertain
@dbu111
3.3K views【Naty.B】, 19:09