አራተኛ ዙር፣ ምዕራፍ ሁለት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ የሚያንቀሳቅሱና ለማንቀሳቀስ የተዘጋጁ እጩዎችን ለማሰልጠን ባደረገው ምዝገባ ከ400 ሺ በላይ ሰልጣኞች የተመዘገቡ ሲሆን በሶስት ምዕራፎች ከፋፍሎ ለማሰልጠን በወሰነው መሰረት በመጀመርያው ምዕረፍ 114 ሺ ቀ ሰልጣኞች እንዲሳተፉበት የተዘጋጀው ስልጠና ቅዳሜ በቀን 18/06/15 ከሰልጣኞች ለተነሱ ወሳኝ ጥያቄዎች በባንኩ ፕሬዚደንት ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) በተሰጡ አመርቂ ምላሾች ተጠናቋል። ይህንን ተከትሎ ሁለተኛና ሶስተኛ ምዕራፍ ስልጠናዎች የሚሰጡበትን ጊዜ አስመልክቶ ጥያቄዎች እየቀረቡ እንደሆነ ታውቋል። በመሆኑም ቀጣይ የ4ኛው ዙር ቀሪ ምዕራፎች/ስልጠናዎች መቼ እንደሚሆኑ ባንኩ ባሉት የሚዲያ አማራጮች የሚያስታውቅ ስለሆነ፣ እንዲሁም ለ2ኛው ምዕራፍ የምትመረጡ ሰልጣኞች ደግሞ በምዝገባ ወቅት ባስመዘገባችሁት ስልክ ቁጥር አማካኝነት ለስልጠናው መመረጣችሁን በቀጥታ እንድታውቁት ስለሚደረግ በትዕግስት እንድትጠብቁ እንጠይቃለን። 31.6K views06:27