2022-07-07 08:44:58
በተከታታይ ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የዳንዲቦሩ ኮሌጅ ደሴ ካምፓስ ዓመታዊ የስፖርት ውድድር በአስገራሚ ሁኔታ የእግር ኳስ እንዲሁም የመረብ ኳስ ውድድር በአንደኛ ዓመት የቢኤስሲ ነርስ ተማሪዎች ዋንጫ ባለቤትነት ተጠናቋል::
በየዓመቱ የሚደረገው የዳንዲቦሩ ኮሌጅ ደሴ ካምፓስ የስፖርታዊ ውድድር ለተከታታይ ሳምንታት ሲደረግ መቆየቱ ይታወቃል በመሆኑም ከብዙ ከባድ እና አዝናኝ ውድድሮች በሆላ በቀን 26/10/2014 ዓ.ም ተጠናቋል::
በመረብ ኳስ መርሀግብር የዋንጫ ጨዋታ 1ኛ ዓመት ነርስ ከ 3ኛ ዓመት ነርስ ጋር የነበረ ሲሆን ጨዋታው ሳቢ እና ልብ አንጠልጣይ ቢሆንም በመጨረሻም በያዝንው ዓመት በ2014 ዓ.ም ወደ ኮሌጃችን የተቀላቀሉት የ1ኛ ዓመት የነርስ ተማሪወች የነገወቹ ሀኪሞች ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ ዋንጫውን ከ3ኛ ዓመት ነርስ ተማሪዎች 3 ለ 1 በማሸነፍ 1ኛ ዓመት ነርስ ተማሪዎች የዋንጫ ባለቤት ሁነዋል::
በእግር ኳስ መርሀግብር የዋንጫ ጨዋታ 1ኛ ዓመት ነርስ ከ 2ኛ ዓመት ነርስ ጋር የነበረ ሲሆን ጨዋታው ከታሰበው በላይ ልብ አንጠልጣይ የሆነ ሲሆን 1ኛ ዓመት ነርስ ተማሪዎች በ 90 ደቂቃ ውስጥ በተማሪ ተፈራ መላኩ አንድ ጎል እና ተማሪ አብዱሰላም አንድ ጎል ያስቆጠሩ ቢሆንም ከ 2ኛ ዓመት ነርስ ተማሪዎች ተማር መዝሙር አንድ ጎል እና ቢኒያም ጌታቸው አንድ ጎል በማስቆጠር አቻ ወይም እኩል የሆኑ ሲሆን በተጨማሪም በጭማሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ውስጥ ምንም ጎል ሳይቆጠር በመቅረቱ ወደ ፔናሊቲ በማምራታቸው በመጨረሻም በፔናሊቲ 1ኛ ዓመት ነርስ ተማሪዎች 3 ለ 1 በሆነ ውጤት የእግር ኳስ እና የመረብ ኳስ ዋንጫ አሸናፊ ሁነዋል::
በመጨረሻም የ2014 ዓ።ም በዳንዲቦሩ ኮሌጅ ደሴ ካምፓስ በተከታታይ ሳምንታት ሲካሄድ የነበረው ውድድር በመረብ ኳስ እና በእግር ኳስ ውድድሮች 1ኛ ዓመት የቢኤሲ ነርስ ተማሪዎች ሻንፒወን(የዋንጫ ባለቤት) በመሆን አጠናቆል::
የ2014 ዓ.ም ዓመታዊ ስፖርት ውድድር በጥሩ ሁኔታ እና በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጋችው የአንበሳውን ድርሻ ለተወጣችሁ የተማሪወች ፕሬዝዳንት እና አባላት ፤ የስፖርት ክበብ ሀላፊ እና አባላቶች ፤የተማሪ ተወካዮች ፤ ዳኛወቻችን፤ የተማሪ ተወካዮች እና በውድድሩ ላይ በጨዋነት ለተሳተፋችሁ ውድ ተማሪዎቻችን ዓመታዊ የኮሌጃችን የስፖርታዊ የውድድር በስኬት እንዲጠናቀቅ የነበራችሁ ተሳትፎ ትልቅ እና የማይረሳ ነበር በዚህ ኮሌጁ ከልብ እያመሰገነ ጨዋነት፤ታዛዥነት፤ሀላፊነት መሸከምን፤ ቁርጠኝነት እና መልካም ስነምግባራችሁ አኩሩቶናል እና ይበል ይቀጥል እንላለን::
ዳንዲቦሩ ኮሌጅ ደሴ ካምፓስ
የዳንዲቦሩ ኮሌጅ ደሴ ካምፓስ ማህበረሰብ በሙሉ በቴሌግራም_አድራሻችን '
=> https://t.me/dandiiborudc
በfacebook_አድራሻችን
=> https://fb.me/DBCDC
ጥያቄ ካለዎት በዚህ ያድርሱን:
=> @DandiiBoruCollegeDC_bot
216 views05:44