Get Mystery Box with random crypto!

Daily News 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ dailynews_et — Daily News 🇪🇹 D
የቴሌግራም ቻናል አርማ dailynews_et — Daily News 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @dailynews_et
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.84K

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-09-26 17:10:04
የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተከበረ ነው

የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በደማቅ ሥነ ሥርዓት እየተከበረ ይገኛል።

በዓሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ የተለያዩ የሃይማኖት አባቶች፣ የፌዴራል እና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የእምነቱ ተከታዮች ተገኝተዋል።

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.4K views14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 15:39:12
የአለም ትልቁ ፊት በኢትዮጵያ ተገኝቷል

በዳውሮ ዞን የማረቃ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ አባይነህ አበራ የአለም ትልቁ ፊት ባለቤት ተብለዋል። አቶ አባይነህ አበራ 25 ሴ.ሜ የሚረዝም ፊታቸው የአለም ትልቁ ወይም ረዥሙ ፊት ነው ተብሎ በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ሰፍሯል።

በዚህም ምክንያት የአፍሪካን ትልቁና ረዥሙ ፊት በሚል የአፍሪካ የድንቃድንቆችን ክብረወሰን በመስበር የክብር የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡አቶ አባነህ በዳውሮ ዞን የማረቃ ወረዳ ነዋሪ ስሆን በንግድና በእርሻ ስራ የሚተዳደር ነው።

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.3K views12:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 12:05:57
ኢትዮ ቴሌኮም አዲሱን ሊድ የተሠኘ ስትራቴጂውን አስተዋወቀ፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ለቀጣዮቹ ሶስት አመታት የሚቆየውን ሊድ የተሠኘውን አዲሱን ስትራቴጂ እና የ2015 በጀት አመት የስራ እቅዱን በዛሬው እለት እያስተዋወቀ ይገኛል።የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ እስከ 2017 የሚያገለግለውን አዲሱን ስትራቴጂ እና የበጀት አመቱን እቅድ ለመገናኛ ብዙሀን እያቀረቡ ነው።

እ.ኤ.አ ከ2019 ጀምሮ እስከ ሰኔ 2022 ድረስ ሲያገለግል የነበረው ብሪጅ የተሠኘው ስትራቴጂ ኩባንያው ብቁ ፤ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ የቴሌኮም ኦፕሬተር ለመሆን እያደረገ ላለው ጉዞ መሠረት የጣለ መሆኑን ወ/ት ፍሬህይወት ተናግረዋል።

ብሪጅ ስትራቴጂ የኩባንያው የሪፎርም ውጤት መሆኑን የገለጹት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ በቆይታው ኩባንያውን በሁሉም የተሠማራባቸው መስኮች ውጤታማ ማድረግ የቻለ እና ከመደበኛ የሲም ካርድ ሽያጭ ባሻገር በሌሎች የቴሌኮም አገልግሎቶች እንዲሰማራ አቅም የፈጠረ ነው ብለዋል።ሊድ ስትራቴጂ ከሐምሌ 2014ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ተደርጓል።

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.3K views09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 11:16:19
ክልሎች ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሀረሪ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎች ለደመራና መስቀል በዓላት የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ክረምት አልፎ በጋ ሲተካ፣ አበቦች በምድር ላይ ፈክተው መዓዛቸውን ሲሰጡ፣ በደመና ተሸፍና የነበረች ፀሓይ ብርሐኗን ፈንጥቃ፣ ክረምቱ ለፀደይ ወራት ስፍራውን በሚለቅበት በዚህ ወቅት እንኳን ለታላቁ የመስቀል በዓል በሠላም አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል፡፡

የመስቀል በዓል በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ በፍቅርና በአንድነት የሚከበር በዓል ከመሆኑም ባሻገር ያለው ለሌለው የሚለግስበት፣ የፍሰሃና የደስታ፣ መተሳሰብና አብሮነት የሚወደስበት ታላቅ በዓል ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.2K views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 10:37:51 መረጃ

ራያ ግንባር አስሜላ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የህውሃት የንዑስ ግንባሩ አዋጊ ከእነ አጃቢዎቹ መደምሰሱ ታውቋል።ስለቡድኑ የሰነድ ማስረጃዎች መገኘታቸውም ተሰምቷል።

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.2K views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 17:40:21 መቐለ

የመቐለ ከተማ ነዋሪ ተቃውሞ እንዳያስነሳ የመስቀል በዓል በመቐለ እንዳያከብር ተከልክሏል!!

አሸባሪውን ህወሓት የመቐለ ከተማ ነዋሪ የመስቀል በዓል እንዳያከብር ከልክሏል።

አሸባሪው ህወሓት የመቐለ ከተማ ነዋሪ የመስቀል በዓል እንዳይከበር የከለከለው፤ ህዝቡ ተቃውሞ እንዳያነሳ ስለሰጋ መሆኑ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

የትግራይ ህዝብ በአሸባሪ ህወሓት ታፍኖ በስቃይ ላይ ያለ ህዝብ ነው። የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ይሄን ተረድቶ የትግራይ ህዝብ ከአሸባሪው ህወሓት የመታደግ ሃላፊነት አለው።

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.5K views14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 11:38:35 የራያ ህዝብ ሰቆቃ!

የህዋሃት/ትህነግ ወራሪ ቡድን ወረራ ከፈፀመባቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው የራያ ግንባር በድኖ በኩል #ሳኒቃት_መድህንአለም ቤቴክርስቲያን በመግባት አምስት ቄሶችን አግቶ ወስዶ ምደና ከምሽጋቸው አስሮቸዉ የነበረ ሲሆን የመከላከያ ሰራዊት ሲደርስበት ሁሉንም ቄሶች ገለዋቸ.ው ሄደዋል::

ይህ ወራሪ ቡድን እየተሸነፈ መምጣቱን ተከትሎ ለህሊና የሚዘገንን ድርጊቶችን እየፈጸመ ሲሆን ይህም በራያ ህዝብ ላይ እያደረሰ ከሚገኘው ዘግናኝ ጭፍጨፋ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል ምንጫችን::

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.6K views08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 11:10:16 <<በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረውን ግጭት በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት በሚደረግ የሰላም ድርድር ለመፍታት ቁርጠኛ ነን>> አቶ ደመቀ መኮንን

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን በኒውዮርክ እየተካሄደ ባለው 77ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር

የኢትዮጵያ መንግስት በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተፈጠረውን ግጭት በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት በሚደረግ የሰላም ድርድር ለመፍታት ቁርጠኛ ናት፣

ከአፍሪካ ሕብረት ውጭ የሚደረግ ሌላ አካሄድ ተቀባይነት አይኖረውም፣

ኢትዮጵያ እየተገበረችው ባለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በበርካታ ቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች ተተክለዋል፣

ኢትዮጵያ ዘላቂነት ያለው የኢነርጂ ሽግግርና የአረንጓዴ እድገት እያስመዘገበች ነው፤ ይህ ተግባሯም እውቅናና ተግባራዊ ድጋፍ ሊቸረው ይገባል፣

አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ጠይቀዋል፣

አፍሪካዊያን ጥያቄያችን ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ ሁልጊዜም ይህን ጥያቄ አጠናክረን እንቀጥላለን፣

የአፍሪካ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን የሚችለው በፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ተገቢው ውክልና ሲኖራት ነው፣

ኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት በማኅበራዊ ፣ ምጣኔ ሀብትና በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ለውጥ አሰመዝግባለች፣

ኢትዮጵያ የዓባይን ግድብ በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ስር በሚደረግ የሦስትዮሽ ድርድር ጉልሕ ተፅዕኖ በማያደርስና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መርህን መሰረት በማድረግ ልዩነቶችን ለመፍታት አሁንም ፅኑ አቋም አላት፣

ሁሉም አገራት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና ወደ ከባቢ አየር የሚለቀቁ በካይ ጋዞችን ለመቀነስ ከአሁን በፊት የገቡትን ቃል ሊተገብሩት ይገባል፣

ዓለም በበርካታ ፈተናዎች እያለፈች ነው፤ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የከፋ ድህነት፣ ግጭት፣ ሽብርተኝነትና ጂኦ ፖለቲካዊ ሽኩቻዎች የባለብዙ ወገን የግንኙነት መድረክን እየፈተኑት መሆኑን ነው፣

የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና ለመከላከል አሰፈላጊውን ፋይናንስ መመደቡ ላይም በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ይገባናል፣

አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ  ምክንያት የሆኑ በካይ ጋዝ ልቀት  ያላት  ድርሻ  ከቁጥር የማይገባ ቢሆንም  ወደ ከባቢ አየር የሚለቀቁ በካይ ጋዟችን ለመቀነስ ግን የተለያዩ ስራዎችን እየከወነች ነው፣

የአየር ንብረት ለውጥ የሚያደርሰውን ጉዳት አስቀድሞ በመተንበይ በትብብር መስራት ይገባናል።
(ኢፕድ)

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.5K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 08:35:44
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የናይጄሪያ አየር መንገድን ለማቋቋም የወጣውን ውድድር አሸነፈ

የአፍሪካ ትልቋ ባለ ብዙ ህዝብ ባለቤት የሆነችው ናይጀሪያ ለበርካታ የአፍሪካ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች የራሷን የአቪዬሽን ተቋም እንዲያቋቁሙላት ጥሪ አቅርባ ነበር።

በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 49 በመቶ ድርሻ በመያዝ የናይጄሪያ አየር መንገድን ለማቋቋም የወጣውን ውድድር ማሸነፉን ሮይተርስ ዘግቧል።

በዚህም መሰረት ናይጄሪያ የራሷ ብሔራዊ አየር መንገድ ባለቤት ለመሆን በሂደት ላይ ስትሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ49 በመቶ ድርሻ ሲኖረው የናይጀሪያ ሉዓላዊ ፈንድ የተባለው ተቋም የ46 በመቶ እንዲሁም የናይጀሪያ መንግስት ደግሞ የአምስት በመቶ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል።

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.3K views05:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 08:10:50
“የቱርክ እና ኢትዮጵያ ግንኙነት አሳስቦኛል”፦ ግብጽ

በቱርክ እና ኢትዮጵያ መካከል የተፈጠረው የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዳሳሰባት ግብጽ አስታውቃ ነበር።

ካይሮ በአንካራ እና አዲስ አበባ መካከል የተፈጠረው ትብብር እንቅልፍ እንደነሳት ለወዳጆቿ አሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት መግለጿን ሮይተርስ የዜና ማዕከል ዛሬ አስነብቧል።

ካይሮ ይሄንን ቅሬታዋን ለአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረት ያቀረበችው አንካራ አዲስ አበባን በወታደራዊ አቅም በተለይም በሰው አልባ የጦር አውሮፕላን /ድሮን/ በገፍ እያስታጠቀች ነው በሚል መሆኑን ሮይተርስ ከ2 የግብጽ የደህንነት የመረጃ ምንጮቼ አገኘው ባለው ዘገባ ላይ ጠቅሷል።

በኢትዮጵያ እና ቱርክ መካከል የተፈጸመ የሰው አልባ የጦር አውሮፕላን /ድሮን/ የግዢ ስምምነት ካለ አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት አስፈላጊውን ማጣራት አድርገው ስምምነቱን ያስቁሙልኝ ሲል የፕሬዝደንት አል ሲሲ መንግስት ደብዳቤ መጻፉንም ዘገባው አንስቷል።

ካይሮ ከአንካራ ጋር ዳግም የሁለትዮሽ ግንኙነት ለመጀመር የምታደርገውን ጥረት የሁለቱ ሀገራት (ኢትዮጵያ እና ቱርክ) ወታደራዊ ስምምነት ሊጎዳው ይችላል ያለው የግብጽ መንግስት ከህዳሴው ግድብ ውዝግብ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ በሰው አልባ የጦር አውሮፕላን /ድሮን/ መጠንከር ካይሮን እንደሚያሳስባት ሮይተርስ ጨምሮ ጠቅሷል።

ምንም እንኳን ከአንካራም ሆነ አዲስ አበባ በኩል በይፋ ማረጋገጫ ባይሰጠውም በሰው አልባ የጦር አውሮፕላን /ድሮን/ ምርት በዓለም ከቀዳሚዎቹ ሀገራት አንዷ ለመሆን የበቃችው ቱርክ ከአፍሪካ አህጉር ሁለት ሀገራትን (ማለትም ኢትዮጵያ እና ሞሮኮን) እያስታጠቀች ስለመሆኑ ሮይተርስ በዘገባው ጠቅሷል።

ሱልጣን አህመድ

@dailyNews_et @dailyNews_et
1.4K views05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ