Get Mystery Box with random crypto!

Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵

የቴሌግራም ቻናል አርማ daily_news_ethiopian — Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵 D
የቴሌግራም ቻናል አርማ daily_news_ethiopian — Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵
የሰርጥ አድራሻ: @daily_news_ethiopian
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.94K
የሰርጥ መግለጫ

Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵
🇪🇹ኢትዮጵያ
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ ቤተሰብ ይሁኑ
Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵
@Daily_News_Ethiopian
አስተያየትና መልክት ካሎት @Natty19
ምርትና አገልግሎቶን ማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን
@Natty19

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-14 15:37:38
በካሚላት መህዲ ላይ አሲድ የደፋው ግለሰብ ከ30 በላይ ሴቶችን በማጭበርበር ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ዋለ!

ከ13 ዓመታት በፊት በካሚላት መህዲ ላይ አሲድ ደፍቶ የግድያ ሙከራ ወንጀል በመፈፀም የሞት ፍርድ ተፈርዶበት በማረሚያ ለ12 ዓመታት ቆይቶ በምህረት የተፈታው ደምሰው ዘሪሁን የማነ፤ አሁን ደግሞ ከ30 በላይ ሴቶችን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሶ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።

ከ13 ዓመታት በፊት በፍቅረኛው ካሚላት መህዲ ላይ አሲድ በመድፋቱ በጥር 21 ቀን 2000 ዓ.ም በተከሰሰበት የግድያ ሙከራ ወንጀል በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሞት ቅጣት የተላለፈበት ደምሰው ዘሪሁን የማነ የተባለው ወይም ራሱን ሳምሶን እያለ የሚጠራው ተጠርጣሪ በወቅቱ ቅጣቱ ወደ የዕድሜልክ እስራት ተሻሽሎለት ማረሚያ ቤት ቢወርድም 12 ዓመት ከ7 ወራት እንደታሰረ እስራቱን ሳይጨርስ በይቅርታ ተለቋል።

ተጠርጣሪው ውሎ ሳያድር በተለያዩ ወንጀሎች ተከሶ ድጋሚ ታስሮ ስለመለቀቁም የፌደራል ፖሊስ ምርመራ ያመለክታል።

ከዚያ በኋላም ተጠርጣሪው ከ30 በላይ ሴቶችን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሶ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል፤ ለአብነትም ነዋሪነቷን በሀገረ ጀርመን አድርጋ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በኮንስትራክሽን ዘርፍ በኢንቨስትመንት በተሰማራችው መሐሪት ክፍሌ ላይ ከባድ የማታለል ወንጀል ስለመፈፀሙ ነው ፖሊስ ያስረዳው።


አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርሶ ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/Daily_News_Ethiopian

https://www.facebook.com/DNEEthiopia
733 viewsedited  12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 14:34:14 የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የካፍ መመዘኛ መስፈርትን ባሟላ መልኩ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ መሪዎች ትኩረት እንዲሰጡት አቶ ኢሳያስ ጅራ ጠየቁ።

የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የአመራር ቁርጠኝነት ከታከለበት የካፍ መመዘኛ መስፈርትን ባሟላ መልኩ በፍጥነት መጠናቀቅ የሚችል መኾኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጅራ ገለጹ፡፡
ባለፉት 15 ዓመታት የሀገሪቱን እግር ኳስ ወደ አንድ ደረጃ ከፍ ሊያደርጉ የሚችሉ ግዙፍ ስታዲየሞች ግንባታ በተለያዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ቢጀመሩም አንዳቸውም መጠናቀቅ አልቻሉም።
ለዓመታት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ሲያስተናግድ የነበረው አንድ ለእናቱ የሚባለው የአዲስ አበባ ስታዲየም ከሶስት ዓመት በፊት በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን እገዳ እንደተጣለበት ይታወሳል፡፡
የስታዲየሙን መታገድ ተከትሎ ባሕር ዳር ስታዲየም በጊዜያዊነት ዓለም አቀፍ ጨዋታ ሲያስተናግድ ቢቆይም የካፍ መመዘኛ መስፈርትን ሙሉ በሙሉ ባለሟሟላቱ ከጥቅምት 2014 ዓም አንስቶ ተመሳሳይ እገዳ ተጥሎበታል።
ይህን ተከትሎም የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድንበ ጨዋታዎችን በመረጠው ሀገር እያደረገ ነው።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ እንዳሉት በሀገሪቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም አለመኖር የተጨዋቾችንና ደጋፊዎችን ስሜት አለፍ ሲልም የኢኮኖሚ አቅምን የሚጎዳ ነው።
በዚህም ብሄራዊ ቡድኑ በሜዳው የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች በሌላ ሀገር እንዲጫወት በመገደዱ ፌዴሬሽኑ ለተጨማሪ ወጪ እየተዳረገ ነው ብለዋል።
በቅርቡ የአማራ ክልል መንግስት የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየምን ግንባታ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ በጀት በመመደብ ግንባታው እንዲቀጥል መፍቀዱ አስደሳች መሆኑን ተናግረዋል።
የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም በሀገሪቱ በጅምር ላይ ከሚገኙ ሌሎች ስታዲየሞች አንጻር የአመራር ቁርጠኝነት ከታከለበት በፍጥነት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የሚችል መኾኑንም ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ኢሳያስ ገለጻ እንደ ሀገር በጅምር ላይ የሚገኙ ስታዲየሞች የዲዛይን ችግር ያለባቸውና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ አለመሆናቸውን ተናግረዋል።
በተለይም ቪአይፒና መደበኛ ትኬት የሚቆርጡ ሰዎች መግቢያ ተመሳሳይ መሆን፣ ጋዜጠኞች ስራቸውን የሚሰሩበት የተመቸ ቦታ አለመኖር፣የተጨዋቾች መኪና የሚገባበት ምቹ መንገድ አለመኖር ክፍተት መሆኑን ነው ያነሱት።
ፌደሬሽኑ ስታዲየሞቹ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲሰሩ በሚደረገው ርብርብ የበኩሉን የቴክኒክ ድጋፍ ይሰጣል ብለዋል። ኢዜአ እንደዘገበው በዚህም ቀጣዩን የአፍሪካ ዋንጫ በምታዘጋጀው ኮቲዲቩዋር የሚገኙ ስታዲየሞችን በመጎብኘት ልምድና ተሞክሮ እንዲወስዱ ከተለያዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ ባለሙያዎች ወደ ሀገሪቱ እንደሚላኩ አቶ ኢሳያስ ተናግረዋል።

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርሶ ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/Daily_News_Ethiopian

https://www.facebook.com/DNEEthiopia
667 viewsedited  11:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 14:34:08
586 views11:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 14:27:39
588 viewsedited  11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 14:26:38
የኃላፊነት ለውጥ አድርገዋል

#Ethiopia : አቶ ዮናስ ሌላ ኃላፊነት እንደተሰጣቸው ተገልጿል። የአዲስ አበባ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮናስ ዘውዴ በሌላ ኃላፊነት ላይ መሆናቸውን ገለጹ። በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች የቢሮ ኃላፊው በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸው እየተገለጸ ነው። አል ዐይን አማርኛ ያነጋገራቸው አቶ ዮናስ ከቢሮ ከወጡ አንድ ወር እንደሆናቸው ገልጸዋል።

አሁን ላይ ከኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊነት ወደ ሌላ የኃላፊነት ቦታ ላይ መዛወራቸውን ተናግረዋል። ይሁንና አሁን አለኝ ያሉትን ኃላፊነት አልገለጹም። አቶ ዮናስ አሁን ላይ የኮሙኒኬሽን ቢሮው በአቶ አብዲ ጸጋዬ እየተመራ መሆኑንም ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል። አቶ ዮናስ ገዥው ብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለአዲስ አበባ ምክር ቤት የተወዳደሩ ሲሆን የም/ቤቱ አባልም ናቸው።

የወቅቱ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲ ጸጋዬ ፤ አቶ ዮናስ ዘውዴ ከኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊነት መነሳታቸውንና ወደሌላ ቦታ መመደባቸውን ለአል ዐይን አረጋግጠዋል።
አቶ አብዲ፤ የቀድሞው የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አሁን የተመደቡበት ቦታ መታወቁንና ደብዳቤውም ቢሯቸው እንደመጣ ገልጸዋል። የወቅቱ የቢሮው ኃላፊ አሁን በስራ ምክንያት ከቢሮ ውጭ በመሆናቸው ወደ ቢሮ ሲመለሱ የአቶ ዮናስን አዲሱን ኃላፊነት እንደሚገልጹ ነው የተናገሩት።

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርሶ ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/Daily_News_Ethiopian

https://www.facebook.com/DNEEthiopia
546 viewsedited  11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 14:25:32
505 viewsedited  11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 14:24:38
558 viewsedited  11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 14:23:39
አሸባሪው ኦነግ ሸኔ በጎረቤት አገራት መደበቁን መንግሥት ገለጸ

የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እየወሰዱ ባለው እርምጃ አሸባሪው ኦነግ ሸኔ ከመዳከም አልፎ ወደ ጎረቤት አገራት በመሸሽ መደበቁን መንግሥት አስታወቀ፡፡

በአሸባሪው ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በተመለከተ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አሸበሪ ቡድኑን ማዳከም መቻሉን አስታውቀዋል፡፡

ቡድኑ እየተወሰደበት ባለው እርምጃ እየተዳከመ ቢሆንም የውሸት መረጃዎችን በማሰራጨት ለጥፋት ሀይሉ ሽፋን የሚሰጡ ግለሰቦች መኖራቸውን የጠቆሙ ሲሆን ሁኔታው በሕዝብ ዘንድ መጠራጠርን ለመፍጠር ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በወለጋ አሸባሪው ቡድን ጥቃት ላደረሰባቸው ዜጎች መንግሥት አስፈላጊውን ደጋፍ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የአሸባሪዎቹ አላማ ከውጭ ባንዳዎች ጋር በመተባበር ሕዝቡ በመንግሥት ላይ ተስፋ እንዲቆርጥ ማድረግ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ህብረተሰቡ ከመንግስት ጋር በመቆም የህግ ማስከበር ዘመቻውን እንዲያግዝ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርሶ ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/Daily_News_Ethiopian

https://www.facebook.com/DNEEthiopia
671 viewsedited  11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 12:53:03
የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ምትኩ ካሳ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ኮሚሽነሩ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው ዛሬ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉት።

በፌደራል ፖሊስ በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ ሀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው ለኢቲቪ እንዳሉት ኮሚሽነሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኤልሻዳይ ከተሰኘ በጎ አድራጎት ማህበር ባለቤት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጅል ፈፅመዋል በሚል በመጠርጠራቸው ነው።

ይህ ኤልሻዳይ የተሰኘ ድርጅት በአዋሽ፣ በአዳማ፣ በሀዋሳ፣ በእንጅባራ በመሳሰሉ አካባቢዎች ተፈናቃዮች በሌሉበት ተፈናቃዮች አሉ በማለት በተደጋጋሚ ጊዜ የእርዳታ እህልና አልባሳት በመረከብ ሽጦ ለተጠርጣሪው መኖሪያ ቤት መግዛቱ በምርምራ መረጋገጡን ነው ረዳት ኮሚሽነር ታደሰ የተናገሩት።

ፖሊስ በተጠርጣሪው ላይ ሰፊ ክትትል ሲያደርግ እንደነበረም ረዳት ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።

Via EBC
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርሶ ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/Daily_News_Ethiopian

https://www.facebook.com/DNEEthiopia
1.0K viewsedited  09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ