Get Mystery Box with random crypto!

ትግራይ፡ የኤርትራ ወታደሮች እንዲወጡ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አቋም መያዙ ተገለጸ የኤርትራ | Ethio 19

ትግራይ፡ የኤርትራ ወታደሮች እንዲወጡ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አቋም መያዙ ተገለጸ

የኤርትራ ሠራዊት ከትግራይ ክልል እንዲወጣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አንድ አይነት አቋም መያዙን የአስተዳደሩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ለቢቢሲ ተናገሩ።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የጽፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረ መስቀል ካሳ እንዳሉት የኤርትራ ሠራዊት በክልላቸው ውስጥ እንዳለ ከመግለጻቸው በተጫማሪ "በክልሉ ውስጥ ያሉ አካባቢዎችን ተቆጣጥረዋል። ወንጀሎችንም ፈጽመዋል" ሲሉ ከስሰዋል።
የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት በትግራይ ክልል የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ የኤርትራ ሠራዊት በክልሉ ውስጥ እንደሚገኝ ቢገልጹም የኢትዮጵያም ሆነ የኤርትራ መንግሥታት ጉዳዩን ሲያስተባብሉ መቆየታቸው ይታወሳል።

የኤርትራ ወታደሮች ትግራይ ውስጥ መኖራቸውን በተመለከተ "ሕዝቡ በዓይኑ ያየው እውነታ ነው" ያሉት አቶ ገብረ መስቀል፤ "ስለዚህም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ወታደሮቹ ከክልሉ መውጣት አለባቸው ሲል አቋም ይዟል" በማለት በአንድ ድምጽ መወሰናቸውን ተናግረዋል።

Link
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa