Get Mystery Box with random crypto!

መቐለን ጨምሮ በትግራይ ክልል የብር ኖት ቅያሬን ከጀመሩ 14 ቀናት ባለፋቸው የክልሉ ከተሞች ሲሰጥ | Addis Merkato

መቐለን ጨምሮ በትግራይ ክልል የብር ኖት ቅያሬን ከጀመሩ 14 ቀናት ባለፋቸው የክልሉ ከተሞች ሲሰጥ የነበረው ቅያሬ እንዲቋረጥ ተወሰነ

ብሔራዊ ባንክ ለአሐዱ ቴሌቪዥን በላከው መግለጫ በክልሉ በነበረው ሕግ የማስከበር ዘመቻ ተቋርጦ የነበረው የብር ኖት ቅያሬ ከታኅሣሥ 21 ጀምሮ ለ14 ቀናት እንዲከወን ከዚህ ቀደም መወሰኑን አስታውሷል፡፡
ሆኖም በአተገባበሩ ላይ ብዥታ ተፈሯል ያለው ብሔራዊ ባንኩ 14 ቀኑ የሚሰላው በአንድ ከተማ ላይ አንድ ባንክ ቀድሞ ሥራ ከሚጀምርበት ቀን አንስቶ ነው ብሏል፡፡

ለምሳሌ በክልሉ አንድ ከተማ ላይ ቀድሞ ሥራ የጀመረው ባንክ ጥር 17 ከሆነ 14 ቀናቱ መሰላት የሚጀምሩት ከጥር 17 ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህም ዘግይተው ሥራ በሚጀምሩት የባንክ ቅርንጫፎች ላይ ተጨማሪ ቀን መስጠት ሳያስፈልግ ቅድሚያ በጀመረው ቅርንጫፍ የጊዜ ገደብ ብቻ እንዲያጠናቅቁ ይገደዳሉ ማለት ነው፡፡