Get Mystery Box with random crypto!

CBE NOOR ሲቢኢ ኑር

የቴሌግራም ቻናል አርማ combankcbenoorofficial — CBE NOOR ሲቢኢ ኑር C
የቴሌግራም ቻናል አርማ combankcbenoorofficial — CBE NOOR ሲቢኢ ኑር
የሰርጥ አድራሻ: @combankcbenoorofficial
ምድቦች: ኢኮኖሚክስ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.91K
የሰርጥ መግለጫ

CBE NOOR is the brand name given to the Interest Free Banking Services of Commercial Bank of Ethiopia. CBE offers full-fledged CBE NOOR Interest Free Banking Services in more than 1,800 branches at window level and in more than 109 dedicated branches.

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-26 06:29:39
633 views03:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 09:43:04
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታውን ዛሬ ያደርጋል፡፡
============================

በታንዛኒያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የሴካፋ ክለቦች ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታውን ዛሬ ከዩጋንዳው ሺ ኮርፖሬት ጋር ያደርጋል፡፡

ቡድኑ በአሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው እየተመራ ምድቡን በአንደኝነት ማጠናቀቁ ይታወቃል፡፡

አምና በመጀመሪያ የሴካፋ ክለቦች ሻምፒዮና ተሳትፎው በሁለተኛ ደረጃ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዘንድሮ የዞኑ ሻምፒዮን በመሆን እ.ኤ.አ በ2022 ማብቂያ በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ለመብቃት ጠንክሮ እየሰራ ነው።
783 viewsedited  06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 17:53:14 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ከ149.8 ቢሊዮን ብር በላይ የፋይናንስ አቅርቦት ማድረጉ ተገለፀ።
===============

ይህ የተገለፀው ዛሬ ነሀሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባብሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚያካሂደው የህዝብ ንቅናቄ እና የሀብት ማሰባሰብ መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ ነው፡፡

በዝግጀቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የግድቡ ሁለተኛ ተርባይን ሃይል ማመንጨት በመጀመሩና የሶስተኛ ዙር የውሃ ሙሌትም በስኬት በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የግድቡን ግንባታ ለዚህ ስኬት ላበቁ አካላት ሁሉም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ባንኩ የተጠናከረ የሀብት ማሰባሰብ ስራ በማከናወን መልሶ ለሃገራችን ልማትና ወሳኝ ለሆኑ ኘሮጀክቶች በማዋል ላይ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ አቤ፣ እ.ኤ.አ እስከ ሃምሌ 31 ቀን 2022 ድረስ ባንኩ ከሀይል ማመንጫ ስራዎች ጋር ለተያያዙ ጉዳዮች ካቀረበው ከ425.2 ቢሊዮን ብር በላይ ፋይናንስ ከ149.8 ቢሊዮን ብር በላይ የሚሆነው ለታላቁ የህዳሴ ግድብ የዋለ መሆኑን ተናግረዋል።

ባንኩ ከሚያደርገው የፋይናንስ አቅርቦት በተጨማሪ በአገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ከተከናወነ የቦንድ ሽያጭ እና በልገሳ በርካታ ገንዘብ በማሰባሰብ ለግድቡ ግንባታ እንዲውል ማድረጉንም ነው አቶ አቤ የገለፁት፡፡

ባንኩ በቅርቡ የ200 ሚሊዮን ብር ቦንድ በስሙ መግዛቱን ያስታወሱት አቶ አቤ፣ የባንኩ ሠራተኞችም ከ19.7 ሚሊዮን ብር በላይ ቦንድ በመግዛት ግንባታው እንዲፋጠን ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡

አቶ አቤ ባንኩ ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ ከሀብት ማሰባሰብ ጀመሮ በሚጠበቅበት ሁሉ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠው፣ ባለድርሻ አካላት በሙሉ በጋራ እንዲሰሩ እና ታላቁን የህዳሴ ግድብ በየትኛውም መንገድ እንዲደግፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በዝግጅቱ ላይ የተገኙት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ የግድቡ ግንባታ 87 ነጥብ 3 በመቶ መጠናቀቁን ገልፀው፣ ቀሪ ስራዎችን በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በእስካሁኑ የግንባታ ሂደት ከ175 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል ያሉት ኢንጂነር ክፍሌ፣ቀሪ ግባታውን ለማጠናቀቅም ከ55-60 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሀብት በማሰባሰብ ሂደት ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ እየተወጡ ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት መካከል አንዱ እና ዋነኛው መሆኑ ተገልጿል፡፡
758 viewsedited  14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 17:53:11
626 views14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 15:41:18
Vacancy
=======
The Commercial Bank of Ethiopia would like to invite qualified and interested job seekers to apply for the following positions:
1. Collateral Valuation Expert- Mechanical Engineer
2. Engineer
3. Legal Advisor
4. IS Auditor - IS Network and Infrastructure Audit
5. IS Auditor - Application System Audit
6. Senior Sanitary Engineer
7. Sanitary Engineer
8. Senior Electrical Engineer
9. Electrical Engineer
10. Mechanical Engineer
11. Architect

Interested and qualified job seekers should apply through CBE career website
(https://vacancy.cbe.com.et ) from August 24 – September 03, 2022.

For requirements and other detail information, please use the following link:
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/EXTERNAL_VACANCY_4d7209e01c.pdf
659 views12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 10:55:28
በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በመካሄድ ላይ ያለውን ኤግኢቢሽን እና ባዛር የመግቢያ ትኬት
በሲቢኢ ብር መተግበሪያ ‘Market Place’ ባሉበት ይቁረጡ!
===================================
የሲቢኢ ብርን መተግበሪያ ሞባይሎ ላይ ለመጫን፡
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡- https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአይፎን ስልኮች፡- https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
624 views07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 17:16:55
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ቻፓ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
=======================
ስምምነቱ ደንበኞችን ሲቢኢ ብርን ጨምሮ ከባንኩ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ጋር በማስተሳሰር የተቀላጠፈ እና ዘመናዊ የክፍያ አገልግሎት ማቅረበ የሚያስችል ነው፡፡

ቻፓ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ (CHAPA Financial Technologies SC) ደንበኞችን የመመልመል፣ ከሲቢኢ ብር እና ከሌሎች የባንኩ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ጋር የማስተሳሰር፣ የ24 ሰዓት የደንበኞች አገልግሎት የመስጠት እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ስራዎችን የሚያከናውን ይሆናል፡፡

በዚህ መሰረት ደንበኞች ጊዜ ቆጣቢ፣ ምቹና እና ቀልጣፋ፣ በጊዜና ቦታ ያልተገደበ በተለያዩ አማራጮች የላቀ የክፍያ አገልግሎት የሚያገኙበት አሰራር ይመቻቻል፡፡

ቻፓ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ የተለያዩ የክፍያ ስርዓቶችን እና አማራጮችን ተግባራዊ ለማድርግ በሀገር አቀፍ የክፍያ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2011 ፈቃድ የተሰጠው ሀገር በቀል ኩባንያ ነው፡፡
781 views14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 13:30:39 CBE NOOR ሲቢኢ ኑር pinned a photo
10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ