Get Mystery Box with random crypto!

የክርስቶስ ደቀመዝሙር ✞

የቴሌግራም ቻናል አርማ christdisciples — የክርስቶስ ደቀመዝሙር ✞
የቴሌግራም ቻናል አርማ christdisciples — የክርስቶስ ደቀመዝሙር ✞
የሰርጥ አድራሻ: @christdisciples
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.08K
የሰርጥ መግለጫ

* ይህ channel ሰለ እውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዝሙርነት ከቅዱሱ መፀሀፍ የሚታይበት ነዉ፡፡
" ማንም መስቀሉን ተሸክሞ በኋላዬ የማይመጣ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም።" ሉቃ 14 : 27

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-15 19:30:52
193 views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 09:26:59
222 views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 00:53:08 #ፈጣኑ_ለውጥ

" ዘኬዎስ ግን ቆሞ ጌታን። ጌታ ሆይ፥ ካለኝ ሁሉ #እኵሌታውን ለድሆች እሰጣለሁ፤ ማንንም በሐሰት ከስሼ እንደ ሆንሁ #አራት_እጥፍ እመልሳለሁ አለው።" (የሉቃስ ወንጌል 19:8)

"8 And Zacchaeus stood, and said unto the Lord; Behold, Lord, the half of my goods I give to the poor; and if I have taken any thing from any man by false accusation, I restore [him] fourfold."
(Luke 19:8)

***
መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ስፍራ ዘኬዎስ ስለተባለ የቀራጮች አለቃ ታሪክ ይናገራል፡፡

ዘኬዎስ ጌታን ለማየት እጅግ ከፍተኛ ጉጉት የነበረው ሰው ሲኾን ጌታን እንዳያይ የሚከልሉትን ነገሮች ኹሉ አልፎ በዛፍ ላይ በመውጣት ጌታን በጉጉት ተመልክቷል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም ፈጣን የሕይወት ለውጥ ካሳዩ ሰዎች መካከልና ኢየሱስን ባገኘ ቀን ሕይወቱና ድርጊቱ የተለወጠ ሰውነው፡፡

የለውጡ ምንጭ ኢየሱስን ለማግኘት የነበረው ጉጉትና ከኢየሱስ የተካፈለው ፍቅር ነበር፡፡ ዛሬም ብዙ ሰው "ክርስቲያን" ነኝ ቢልም የተለወጡ ግን ጥቂቶች ናቸው፡፡ የዘኬዎስ ታሪክ ብዙ የሚያስተምረን ይመስለኛል፡፡
የእኛ ጉጉት
የተካፈልነው ፍቅር

@Christdisciples
587 views21:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 07:58:43 “#ሕግ_በሙሴ በኩል ተሰጥቶ ነበር፤ #ጸጋና እውነት ግን #በኢየሱስ ክርስቶስ #በኩል_መጣ።”
— ዮሐንስ 1፥17

✿ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለተቀበለ ሰው እውነተኛ የምስራች #ወንጌል ብቻ ነው። በምድር ላይ የትኛውም የምስራች ከወንጌል ውጭ እውነተኛ የምስራች አይደለም ሁሉም ሀላፊ ጠፊ ነው፡፡ ወንጌል ግን የዘላለም ህይወት ያገኘንበት ዘላለማዊ ነው ።

@Christdisciples
495 views04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 20:41:55 #የእግዚአብሔር_ስራ_በችግራችን_ይገለጥ

(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 9)
2፤ ደቀ መዛሙርቱም። መምህር ሆይ፥ ይህ ሰው ዕውር ሆኖ እንዲወለድ ኃጢአት የሠራ ማን ነው? እርሱ ወይስ ወላጆቹ? ብለው ጠየቁት።
3፤ ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰ። የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ እንዲገለጥ ነው እንጂ እርሱ ወይም ወላጆቹ ኃጢአት አልሠሩም።


(John 9)
2 And his disciples asked him, saying, Master, who did sin, this man, or his parents, that he was born blind?
3 Jesus answered, Neither hath this man sinned, nor his parents: but that the works of God should be made manifest in him.

***
በዮሐንስ ወንጌል ይህን መሰል ሀሳብ በ ምዕራፍ 11 : 4 ላይም እናገኛለን " ኢየሱስም ሰምቶ። ይህ ህመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ ይከብር ዘንድ ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም አለ።"

ኢየሱስ በእነዚህ ኹለት ስፍራዎች እንዴት ለሰዎች ከባድና ችግር የኾነባቸውን ነገር ለእግዚአብሔር ግን ሥራውንና ክብሩን መግለጫው እንደኾነ ሲያሳያቸው እናነባለን፡፡


ዛሬም በሕይወታችን የበዙ የተለያዩ ችግሮች ይኖራሉ፡፡ እነዛም ችግሮች ሰቅዘው አላስኬድ ብለው ይዘውን እንዲሁም ሕይወታችንን ሙሉ አመሰቃቅለው ሊሆን ይችላል፡፡ ደግሞም በሀዘን አቆራምተው ሕይወትን አጨልመው ይኾናል፡፡ ግን ከነ ድካማችን፣ ሀዘናችንና ችግራችን ወደ ክርስቶስ እየተመለከትን "ጌታ ኾይ በችግሬ ላይ አንተ ክበር" እንበለው

ኢየሱስ ወደእኛ ሲቀርብና በአጠገባችን ሲያልፍ የኛ ችግር ለእሱ ክብር መገለጫ ይኾናል፡፡
መልካም ሳምንት!
@christdisciples
523 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 22:12:22 #ያለኢየሱስ_ምንም_ነኝ

" እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። #ያለ_እኔ_ምንም_ልታደርጉ_አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።"
(የዮሐንስ ወንጌል 15:5)

"5 I am the vine, ye [are] the branches: He that abideth in me, and I in him, the same bringeth forth much fruit: #for without_me_ye_can_do_nothing."
(John 15:5)

***
የክርስትና ሕይወት የተመሠረተው በኢየሱስ ላይ ነው፡፡ መሠረታችንም እርሱ ነው፡፡ እኛ የክርስቶስ ደቀመዝሮች የተጣበቅንበት ግንድ ኢየሱስ ይባላል፡፡

አንዳንድ ጊዜ ግን ግንዱን ኢየሱስን ትተን በራሳችን አቅም ፣ ችሎታ፣ መልካምነት ለመፍጨርጨር እንሞክራለን። ይህ ግን ከንቱ ድካም ነው፡፡ ማንኛውም ቁጥር በዜሮ ቢባዛ ዜሮ እንደሆነ የኛም መንፈሳዊ ሕይወት ያለ ኢየሱስ ባዶ ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢየሱስ አስቀድሞ ያለ እኔ ምንም ማረግ አትችሉም ያለው፡፡

ስለዚህ ምን እናድርግ?
ሁልጊዜ ለኢየሱስ "ያላንተ ምንም ነኝ" እንበለው ። ከነድካማችንና ከነሀጢያአታችን በፀጋው ፊት ወድቀን "ያላንተ ምንም" ነኝ እንበለው፡፡

@Christdisciples
584 views19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 22:00:59 #ከባርነት_መለቀቅ

" እግዚአብሔርም ሙሴን ተናገረው። ወደ ፈርዖን ግባ እንዲህም በለው። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ያገለግለኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ።"
(ኦሪት ዘጸአት 8:1)

"1 And the LORD spake unto Moses, Go unto Pharaoh, and say unto him, Thus saith the LORD, Let my people go, that they may serve me."
(Exodus 8:1)

**
እግዚአብሔር በባርነት ለያዘን ነገር ሁሉ ዛሬም ልጆቼን ያገለግሉኝ ዘንድ ልቀቅ ይላል። ከሕይወታችን ተጣብቆ የያዘን የኀጢት ስርና የአለም ምኞትን ልቀቅ ይለዋል፡፡

ነገር ግን እኛ ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር ወደሚወስደን የነፃነት ምድር ስንጓዝ የፈርዖን አገዛዝንና የፈርዖን ምድርን እንሻለን፡፡ እግዚአብሔር በበረሀ በተዓምር ከሚመግበን መና ይልቅ የግብፅ ሽንኩርት ይናፍቀናል፡፡ ብዙዎች እስራኤራዊያን በበረሀ የቀሩት በዚህ ሀሳባቸው ነው፡፡

ወደ ነጻነታችን ስንጓዝ እግዚአብሔርን ፈፅመን እንመነው ዛሬም ያዘኝ አጥብቀህ እንበለው


እጄን ያዘኝ ጌታ ፣ እጄን ያዘኝ
እጄን ያዘኝ ኢየሱስ ፣ እጄን ያዘኝ

ያለማመኔን ደካማነቴን አግዘህ በፍቅርህ
እድፍ ቁሸቴን አጥርተህ
ባንተ ነው ከረግረግ ውስጥ መውጣቴ
በመቆም የተቀየረው ሕይወቴ

------

የቆምኩ ሲመስለኝ መውደቅ አለና
ሁሉን አሻግረኝ በእጅህ ያዝና ...

@Christdisciples
522 views19:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 21:01:35 ጽናትና ውሳኔ

(መጽሐፈ ሩት ምዕራፍ 1)
----------
12፤ ልጆቼ ሆይ፥ ተመለሱ፤ ባል ለማግባት አርጅቻለሁና ሂዱ፤ ተስፋ አለኝ ብል፥ ዛሬ ሌሊትስ እንኳ ባል ባገባ፥ ወንዶች ልጆችም ብወልድ፥

13፤ እነርሱ እስኪያድጉ ድረስ ትቆያላችሁን? ስለ እነርሱስ ባል ማግባት ትተዋላችሁን? ልጆቼ ሆይ፥ እንዲህ አይደለም፤ የእግዚአብሔር እጅ በእኔ ወጥቶአልና ከእናንተ የተነሣ እጅግ ተመርሬአለሁ።

14፤ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው እንደ ገና አለቀሱ፤ ዖርፋም አማትዋን ሳመች፤ ሩት ግን ተጠጋቻት።

15፤ ኑኃሚንም። እነሆ፥ ባልንጀራሽ ወደ ሕዝብዋና ወደ አማልክትዋ ተመልሳለች፤ አንቺም ደግሞ ከባልንጀራሽ ጋር ተመለሽ አለቻት።

16፤ ሩትም። ወደምትሄጅበት እሄዳለሁና፥ በምታድሪበትም አድራለሁና እንድተውሽ ከአንቺም ዘንድ እንድመለስ አታስቸግሪኝ፤ ሕዝብሽ ሕዝቤ፥ አምላክሽም አምላኬ ይሆናል፤

17፤ በምትሞችበትም ስፍራ እሞታለሁ፥ በዚያም እቀበራለሁ፤ ከሞት በቀር አንቺንና እኔን አንዳች ቢለየን እግዚአብሔር ይህን ያድርግብኝ እንዲሁም ይጨምርብኝ አለች።

18፤ ኑኃሚንም ከእርስዋ ጋር ለመሄድ እንደ ቈረጠች ባየች ጊዜ እርስዋን ከመናገር ዝም አለች።

"14 And they lifted up their voice, and wept again: and Orpah kissed her mother in law; but Ruth clave unto her."
(Ruth 1:14)

**

በዚህ የሩት መጽሐፍ ውስጥ ድንቅ ታሪክ እናነባለን፡፡ እሱም እንዴት አንዲት ሴት የወሰነችው ቁርጥ ውሳኔ ሕይወቷን ለዘላለም እንደቀየረው ነው፡፡

በዚህ ምድር ኹላችንም የምንኖረው የውሳኔዎቻችንን ፍሬ ነው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ነገሮችን በጽናት ሳይኾን በስሜት ስንወስን ብዙ ዎጋ እንከፍልባቸዋለን፡፡

ከሩት የጸና የአልመለስም ውሳኔ ምን እንማለን
****
ሩት በውሳኔዋ በመጽናቷ ከአህዛብ ወገን ኹና ሳለ - የኢየሱስን ዘር ትውልድ ተቀላቀለች

ሩት የኑሀሚንን ችግር ሳታይ በእምነት ስለተከተለቻት የእስራኤል አምላክ ህይወቷን በበረከት አትረፈረፈው

ሩት ጸንታ ኑሀሚንን በመከተሏ ታሪኳ ዘላለማዊ ኾነ ዖርፋ ግን ከዛ በኀላ ምን እንደደረሰባት ራሱ አይታወቅም

ሩት ያመነችው ኑሀሚንን ሳይኾን የሳን አምላክ ነበር እና በውሳኔዋ እምነቷን ገለጠች አምላክም መልሶ ታመነላት

ዛሬስ እኛ በሕይወታችን የጸናንባቸው ውሳኔዎች ምንድን ናቸው?
ምን ያህል ነገሮችን ሁሉ አልፈን ሳንመለስ በጽናት ጌታን እየተከተልነው ነው?
***
ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት በመጽናት ወደኀላ ላንመለስ ጌታን ይዘን መከተል ይኹንልን፡፡ ሩት ወደ ኑሀሚን በእምነት እንደተጠጋች እኛም ዘወትር ወደ ጌታ መጠጋት ፣ ወደሱ መቅረብ ይኹንልን
560 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 19:07:19 ጭንቀት ምንድነው? አለማችን በብዙ ጭንቀት ተሞልታለች ፣ ታዲያ እኛ ምን እናድርግ?
የኑሮ ውድነት ፣ የህመም ፣ የጦርነት ወሬ እንዲሁም ሌሎች ሁኔታዎች የሚያስከትሉትን ጭንቀት እንዴት እናሸንፋለን?
ይሄን ቪዲዬ ብትሰሙ ቡዙ ቁምነገር ትገበያላችሁ
ለሌሎችም ያጋሩ


477 views16:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:05:51 -Leaving Egypt Behind

" የእስራኤልም ልጆች ሁሉ በሙሴና በአሮን ላይ አጕረመረሙ፤ ማኅበሩም ሁሉ። በግብፅ ምድር ሳለን ምነው በሞትን ኖሮ! ወይም በዚህ ምድረ በዳ ምነው በሞትን ኖሮ! "
(ኦሪት ዘኍልቍ 14:2)

"2 And all the children of Israel murmured against Moses and against Aaron: and the whole congregation said unto them, Would God that we had died in the land of Egypt! or would God we had died in this wilderness!"
(Numbers 14:2)

**

በዚህ ስፍራ እስራኤላዊያን እግዚአብሔር ወዳዘጋጀላችው የተስፋይቱ ምድር ሲጓዙ የገጠማቸውን ነገሮች እንመለከታለን፡፡ ሕዝቡ በ ምዕራፍ 13 ላይ በሰሙት አሉታዊ ሪፖርት ምክኒያት ፈርተው፣ ተሸብረው ለነፍሳቸው ሰግተው ከተስፋይቱ ምድር ይልቅ ወደኀላ የባርነት ዘመን መመለስን ናፍቀዋል፡፡

እኛም በሕይወታችን ከዙሪያችን ካሉ ሰዎች በምንሰማቸው መጥፎ ነገሮችና ከሚገጥሙን ችግሮች የተነሳ እግዚአብሔር ካዘጋጀልን የተስፋ ምድርና ቃል ብዙ ጊዜ እምነት በማጣትና ስጋዊ በኾነ ሀሳብ በመታሰር ወደፊት ከመገስገስ ወደኀላ መመለስን እንሻለን፡፡ ሰይጣንም እግዚአብሔር ወዳዘጋጀልን ከፍታ እንዳንደርስ በዙሪያችን ብዙ አሉታዊ ሰዎችን ያሰማራል፡፡

ወደ ሀገራችንም ስንመለከትና ቆም ብለን ስናስብ የሀገራችን የሕዝብ ኹኔታ እንዲህ የኾነ ይመሰልላል፡፡ ብዙ ሰው በፍርሀትና ተስፋ በመቁረጥ የቀደመውን ነገር ይናፍቃል፡፡

****

አላማኞች ኹልጊዜ በበረሀ ይቀራሉ አልያም ወደኀላ ተመልሰው ዳግም በግዞት ይኖራሉ፡፡
እኛ ግን ማወቅ ያለብን ነገር የሚመጣውና ተስፋ የተገባልን ምድር ከቀደመው እጅግ የሚልቅና አሁን የምናልፍበትን አባጣ ጎርባጣ መንገድ የሚያስረሳ ነው፡፡ ስለዚህ እንደ እግዚአብሔር ቃል የተገባልንን የተስፋ ምድር በእምነት ለመውረስ እንትጋ፡፡
***
ዘወትር የእግዚአብሔርን ተስፋ ቃል በማመን በመንፈስ መመላለስና ወደተገባልን የተስፋ ምድር በእምነት መገስገስ ይኹንልን
471 viewsedited  18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ