#JimmaUniversity
በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡ የጅማ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የሥራ ርክክብ አድርገዋል።
ነባሩ የሥራ አመራር ቦርድ ያከናወናቸው ሥራዎች፣ የገጠሙት ፈተናዎች እና በጅምር ላይ የሚገኙና በቀጣይ የሚከወኑ ሥራዎች ላይ ውይይት ተደርጓል።
የአዲሱ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ መሆናቸው ይታወቃል።
በጤና ሚኒስቴር በተከናወነው የሥራ ርክክብ፤ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) ለነባሩ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የምስክር ወረቀት እና የምስጋና ስጦታዎችን አበርክተዋል።
@campus_group_ethiopia
@campus_group_ethiopia