Get Mystery Box with random crypto!

የአማኞች ጋሻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ byshakheliyasahmed — የአማኞች ጋሻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ byshakheliyasahmed — የአማኞች ጋሻ
የሰርጥ አድራሻ: @byshakheliyasahmed
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 43

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2019-12-18 18:17:15 ፡፡

ሌሎችንም የተውሒድ ዕውቀት ለመሠብሠብ join


በ telegram

t.me/sadamnassirr s.


በዋትሳት

https://chat.whatsapp.com/Dyebl8aTWjmDeTcIBrdoC3
128 views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-18 18:17:14 #የአማኞች ጋሻ
#ክፍል 60

#ታሪካዊ.ውይይት


“ቁርኣን ፍጡር ነው!” የሚለውን የአላህን የመናገር ባህሪ የሚያፋርስ የክህደት አቋም ባለመቀበላቸው ታስረው የነበሩ አንድ በእድሜ ጠና ያሉ ዓሊም ከአሕመድ ኢብን አቢ ዱኣድ(1) ጋር ኸሊፋው አል-ዋሢቅ (232 ዓ.ሂ) ባለበት ያደረጉትን ምልልስ በአጭሩ እንደሚከተለው አቀርበዋለሁ፦

ኸሊፋው ለዓሊሙ፦] “ከአሕመድ ኢብን አቢ ዱኣድ ጋር ተወያዩ!”…




- [ዓሊሙ፦] “አሚሩ’ል-ሙእሚኒን ሆይ! የምንመላለሳቸውን ቃላት በደንብ ብታስተውልልን..?”
- [ኸሊፋው፦] “እሺ!”
- [ዓሊሙ ለኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “ይህ ሰዎችን ወደ እርሱ የምትጣራው (የቢድዓህ) ንግግርህ የዲን እምነት ወስጥ የሚካተት ግዴታና ያለ እርሱ ዲን የማይሞላ ነውን?”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “አዎን!”




- [ዓሊሙ፦] “አላህ መልዕክተኛውን (ﷺ) ወደ ባሮቹ ሲልክ እርሳቸው እንዲያስተላልፉ ከታዘዙት የዲን ጉዳይ የሸሸጉት ነገር አለ?”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “የለም”!
- [ዓሊሙ፦] “ታዲያ መልዕክተኛው (ﷺ) ወደዚህ ንግግርህ ተጣርተዋል?!”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] (ፀጥ!)(2)


- [ዓሊሙ፦] “ተናገር እንጂ!”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] (አሁንም ፀጥ!)


- [ዓሊሙ ለኸሊፋው] “አሚሩ’ል-ሙእሚኒን ሆይ! አንድ (ብለህ ቁጠርልኝ)!”
- [ኸሊፋው፦] “አንድ!”

[ዓሊሙ ለኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “ማነው እውነተኛው? ሀይማኖታችንን እንዳሟላልን የነገረን[አል-ማኢዳህ 3] አላህ? ወይስ ይህንን መጤ ንግግርህን እስክናምን ድረስ ጎዶሎ እንደሆነ የነገርከን አንተ?!”


- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] (ፀጥ!)
- [ዓሊሙ፦] “መልስልኝ!”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] (አሁንም ፀጥ!)


- [ዓሊሙ ለኸሊፋው] “አሚሩ’ል-ሙእሚኒን ሆይ! ሁለት በልልኝ!”


- [ኸሊፋው፦] “ሁለት!”


- [ዓሊሙ ለኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “እስቲ ንገረኝ! ይህንን ንግግርህን መልዕክተኛው አውቀውት ነበር ወይስ አላወቁትም?”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “አውቀውታል!”
- [ዓሊሙ፦] “ሰዎችን ወደዚያ ጠርተዋል?”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] (አሁንም ፀጥ!)
- [ዓሊሙ ለኸሊፋው] “አሚሩ’ል-ሙእሚኒን ሆይ! ሶስት በልልኝ!”


- [ኸሊፋው፦] “ሶስት!”


- [ዓሊሙ ለኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “እንደምትለው የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) ይህንን እያወቁት ተከታዮቻቸውን ወደዚህ ባለመጣራታቸው ተብቃቅተዋል?”
- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “አዎን!”
- [ዓሊሙ፦] “አቡ በክር፥ ዑመር፥ ዑሥማንና ዐሊይም እንደዚሁ በዝምታ ተብቃቅተው ነበር?”



- [ኢብኑ አቢ ዱኣድ፦] “አዎን!”


ዓሊሙ ወደ ኸሊፋው በመዞር፦] “ረሱልን (ﷺ) አቡ በክርን፥ ዑመርን፥ ዑሥማንንና ዐሊይን ያብቃቃቸው ዝምታ የማያብቃቃህ ከሆነ፦ ለነሱ የተመቻቸው የማይመቸው ሁሉ አላህ ምቾትን ይንሳው!”




- [ኸሊፋው፦] “አዎን! ረሱልን አቡ በክርን፥ ዑመርን፥ ዑሥማንንና ዐሊይን ያብቃቃቸው ዝምታ የማያብቃቃን ከሆነ፦ ለነሱ የተመቻቸው የማይመቸው አላህ ምቾትን ይንሳው!!” ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ኸሊፋው የግል አቋሙን እንዳስተካከለ ይነገራል!(3)







#ክፍል.ስምንት


#እውነታውን.ለተፃረሩት.ያለን.ምልከታ

ትክክለኛውን የእምነት ጎዳና የሚስቱ ሁሉ አንድ ወጥ ብይን የሚመለከታቸው አይደሉም።
ሸይኹ'ል-ኢስላም ኢብኑ ተይሚይ-ያህ እንዲህ ይላሉ፦

«..እንዲሁም ሊታወቅ የሚገባው ነገር በሀይማኖት መሠረቶችና በ“ከላም” ወደተለያዩ መሪዎች ራሳቸውን የሚያስጠጉ ጭፍራዎች በተለያዩ ደረጃዎች ላይ መሆናቸው ነው፦ ከነርሱ መካከል በታላላቅ መሠረቶች ላይ ትክክለኛውን ፈለግ የተፃረረ አለ፤ ከነርሱ መካከል ደግሞ ትክክለኛውን ፈለግ የጣሰው በውስብስብ ጉዳዮች ላይ የሆነ ይኖራል…»(4)




የአላህን መገለጫዎች በተመለከተው ታላቅ ርዕሰ-ጉዳይ ላይ ግልፅ ጥመትን ያራቡ የነበሩት የመጀመሪያዎቹ የጀህሚይ-ያህ አቀንቃኞች ሰለፎች ዘንድ በጥቅል እይታ እንደ ከሃዲያን ይታዩ ነበር።(5)
ምክንያቱም ግልፅ ማስረጃዎችን በማስተባበል ሁሉንም የፈጣሪን ስሞችና ባህሪያት ከመሠረቱ በማፋረሳቸው ነው። ሆኖም በነሱ ተፅእኖ ስር ያደሩት ሁሉ የግድ በዚህ እይታ የሚገመገሙ አይደሉም! ሸይኹ'ል-ኢስላም ኢብኑ ተይሚይ-ያህ ስለ ፅንፈኛዎቹ ጀህሚይ-ያዎች እንዲህ ይላሉ፦

«ንግግራቸው በሶስት ጎኖች አስከፊነቱ ይገለፃል፦ አንደኛ፦ ንግግራቸውን የሚቃረኑ የቁርኣን፣ የሐዲሥና የኢጅማዕ ማስረጃዎች እጅግ ብዙና የታወቁ ናቸው። ሆኖም እነዚህን የሚመልሷቸው በማጣመም ነው! ሁለተኛው፦ የንግግራቸው እውነተኛ ገፅታ የፈጣሪን ህልውና ማስተባበል ነው - ምንም እንኳ ከነርሱ መካከል የንግግራቸው ውጤት የፈጣሪን ህልውና ማስተባበል መሆኑን የማያውቅ ቢኖርም! እምነት በመሠረታዊ እይታ በአላህ ማመን እንደሆነው ሁሉ ክህደትም በመሠረታዊ እይታ አላህን መካድ ነው። ሶስተኛው፦ እነርሱ ሁሉም የእምነት መንገዶችና የንፁህ ተፈጥሮ ባለቤቶች የሚስማሙባቸውን እውነታዎች ይፃረራሉ! ሆኖም ይህ ከመሆኑ ጋር የብዙ ንግግሮቻቸው እውነተኛ ገፅታ ከብዙ የኢማን ባለቤቶች ሊሰወር ይችላል - በሚያቀርቡት ውዥንብር የተነሳ እውነቱ ያለው እነርሱ ዘንድ እስኪመስለው ድረስ! ከመሆኑም ጋር እነዚያ አማኞች በግልፅም በድብቅም በአላህና በመልዕክተኛው የሚያምኑ ይሆናሉ። ይህ የተምታታባቸውና የተመሳሰለባቸው ልክ ሌሎች የተለያዩ የቢድዓህ ሰለባዎች (እውነታው) እንደተምታታባቸው ነው! በርግጠኝነት እነዚህ ከሃዲያን (ካፊሮች) አይደሉም! ይልቁንም ከነርሱ መካከል አመፀኛና ወንጀለኛ የሚሆን ይኖራል፤ እንዲሁም የተሳሳተና ጥፋቱ የሚማርለት ይኖራል፤ ምናልባትም ኢማንና ተቅዋ (የአላህ ፍራቻ) ያለውና በዚያው ልክም የአላህን ወዳጅነት የሚጎናፅፍ ይኖራል!»(6)




(1) ይህ የጀህሚይ-ያህ አቀንቃኝ አል-ኢማም አሕመድን ለማስገደል ሲጥር የነበረ የሱን-ናህ ቀንደኛ ጠላት ነው!

(2) “አዎን!” ካለ በምንም መረጃ ሊደግፈው የማይችል አይን ያፈጠጠ ቅጥፈት ስለሚሆን ነው ዝም ያለው! መልዕክተኛው (ﷺ) ወደ ተዕጢል ተጣርተዋል ብሎ የሚሞግት ካለ የምላሱን ቅጥፈት ልቦናው ያውቀዋል!


(3) “አሽ-ሸሪዓህ” ሊ’ል-ኣጁር-ሪይ ገፅ 91፣ “ታሪኹ በጝዳድ” ሊ’ል-ኸጢብ (11/271)፣ “አል-ኢባናህ” ሊ’ብኒ በጥ-ጣህ (2/269)፣ እና ሌሎች መዛግብት ላይ ሰፍሯል።

(4) “መጅሙዑ’ል-ፈታዋ” (3/348)




(5) ይህን እውነታ ያስተላለፉ በርካታ መዛግብት አሉ። ለምሳሌ፦ አል-ኢማም አል-ላለካኢይ (418 ዓ.ሂ) የቁርኣንን የአላህ ንግግር መሆን =>=> ለማስተባበል “ፍጡር ነው!” የሚሉትን ጀህሚይ-ያዎች በጥቅሉ በከሃዲነት
የፈረጁ በርካታ የሰለፍ ሊቃውንትን ከዘረዘሩ በኋላ እንዲህ ይላሉ፦

«እነኚህ ከደጋጎቹ ሰሓቦች ውጪ ያሉ ዘመናቸው ከመለያየቱና አመታት ከመተካካታቸው ጋር ከታቢዒዮች፣ ከነርሱ ተከታይ ትውልዶችና ከ(ሌሎች) ተወዳጅ ኢማሞች (የተውጣጡ) አምስት መቶ ሃምሳ ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑ ነፍሶች ናቸው! በውስጣቸውም ሰዎች ንግግራቸውን ይዘው መዝሃቦቻቸውን የሚከተሉ የሆኑ መቶ ያህል ኢማሞች ይገኛሉ! የቅርብ ጊዜዎቹን (ዓሊሞች) ንግግሮች በማጣቀስ ብጠመድ ኖሮ ስሞቻቸው ብዙ ሺዎች በደረሱ ነበር!» [“ሸርሑ ኡሱሊ’ዕቲቃዲ አህሊ’ስ-ሱን-ናህ” ሊ’ል- ላለካኢይ (2/344)]

6) “መጅሙዑ’ል-ፈታዋ” (3/354-355)

ኢንሻኣላህ ቀጣይ

በተወዳጅ የሱና ኡስታዞቻችን የተፃፉ መፅሐፎች ለማግኘት
139 views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-14 10:49:27 በአላህ ፍቃድ #ተውሒድ የተሰኘው መፅሐፍ ተጠናቋል።
ኢንሻአላህ በምትኩ ሌላ እንጀምራለን ብዬ ተስፋ አረጋለሁ።
ይህ መፅሐፍ #ሙሉውን ወይም ከክፍል #አንድ እስከ ክፍል #ሀያ.ሶስት ለማግኘት
በዚህ ሊንክ #link ግቡና አንብቡ።

@yetewhidmetsaf
@yetewhidmetsaf
t.me/yetewhidmetsaf
127 views07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-11 18:35:25 ው አቀርበዋለሁ፦




(1) በምዕራፍ አንድ ላይ የመጀመሪያውን መርሆ ማብራራያ ደግመው ቢያዩት
ይበልጥ ይጠቀማሉ!

(2) ከአሽዐሪይ-ያህ ታላላቅ አቀንቃኞች አንዱ የሆነው አስ-ሰኑሲ (895 ዓ.ሂ)
“የክህደት /የኩፍር/ መሠረቶች ስድስት ናቸው..” ብሎ አምስቱን ዘርዝሮ
ስድስተኛውን እንዲህ ሲል ገለፀ፦ “በእምነት መሠረቶች ላይ የቁርኣንና
የሐዲሥ ጉልህ መልዕክቶችን በአእምሯዊ ማስረጃዎችና በቁርጠኛ ሸሪዓዊ
እውነታዎች ሳይመዝኑ እንዳሉ መያዝ..”!! [“ሸርሑ ኡም-ሚ’ል-በራሂን”
ገፅ 81] እንደዚሁም አስ-ሷዊ እንዲህ ይላል፦ “..የቁርኣንና የሐዲሥ ጉልህ
መልዕክቶችን መያዝ ከኩፍር መሠረቶች ነውና!”!![“ሓሺየቱ’ስ-ሷዊ ዓላ
ተፍሲሪ’ል-ጀላለይን” (3/9)]

(3) ይህ የጀህሚይ-ያህ አቀንቃኝ አል-ኢማም አሕመድን ለማስገደል ሲጥር የነበረ
የሱን-ናህ ቀንደኛ ጠላት ነው!






ኢንሻአላህ ደስየሚል ውይይት ነው ቀጣይ እንገናኝ
እናንተ ጆይን በሉ ግቡ


በተወዳጅ የሱና ኡስታዞቻችን የተፃፉ መፅሐፎች ለማግኘት፡፡

ሌሎችንም የተውሒድ ዕውቀት ለመሠብሠብ join


በ telegram

t.me/sadamnassirr s.
@Byshakheliyasahmed

በዋትሳት

https://chat.whatsapp.com/Dyebl8aTWjmDeTcIBrdoC3
119 views15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-11 18:35:25 #የአማኞች.ጋሻ
#ክፍል 59

#ክፍል ሰባት

#የማንቂያ.ደወል!

በቁርኣንና በትክክለኛ ሐዲሦች በግልፅ ሂደት የፀደቁትን የአላህ
ስሞችና ባህሪያት ለርሱ ልቅና በሚገባ መልኩ እንዳሉ ማረጋገጥ
አማራጭ የሌለው ግዴታ መሆኑ በተለያዩ ማስረጃዎች
ተብራርቷል!
ይሁንና አብዛኛዎቹን የአላህ መገለጫዎች ለፈጣሪ የማይገባ
ጉድለትን እንደሚያንፀባርቁ በማመን ሳይታክቱ አንድ በአንድ
የሚያፋርሱና ትርጓሜያቸውንም የሚጠመዝዙ ጎራዎች እንዳሉ
አውቀናል። ይህ አካሄዳቸው በተዘዋዋሪ የሚያንፀባርቀው መልዕክት
እጅግ አደገኛ ነው! ሆኖም አብዛኛዎቹ አይረዱትም!
 ከዚህ በፊት እንደተገለፀው የአንድ ተናጋሪ ንግግር በተወሰኑ
ርዕሶች ላይ ሁል ጊዜ አሻሚና የተድበሰበሰ የሚሆነው፦
- ወይ ስለ ጉዳዩ ካለው እውቀት ማነስ ነው፤
- ወይ ደግሞ ከአገላለፅ ችሎታው ማነስ ነው፤
- አሊያም እውነታውን የመግለፅ ፍላጎት (ቅንነት) ካለመኖር ነው!

ከእነኚህ ሶስት እንከኖች አንዱም በአላህና በመልዕክተኛው ንግግር
ወስጥ ፍፁም ሊኖር እንደማይችል ደግሞ የማይታበል እውነታ
ነው።(1)
በዚህ መሠረት እነዚያ የ‘ተዕጢል’ አራማጆች ካሉበት ሰመመን
ይነቁ ዘንድ የሚከተሉትን ጥያቄዎች እናቀርብላቸዋለን፦
1- የቁርኣን አንቀፆችና የመልዕክተኛው አስተምህሮቶች እነዚያን
የተለያዩ የአላህ ባህሪያት ደግመው ደጋግመው በሚያፀኑ የተለያዩ
አገባቦች የሚያወሱት ለምንደነው?
1.1- አላህና መልዕክተኛው ለጌታ የሚገባውን መገለጫ
‘እንደናንተ’ የማያውቁ ሆነው ነው?!
1.2- ወይስ እናንተ በምታዘወትሯቸው ቃላት እውነታውን
መግለፅ ተስኗቸው?!
1.3- ወይስ ሆን ብለው ጉዳዩን በማድበስበስ ሙስሊሞችን
ለማሳሳት ነው?!
መልሳችሁ “አረ በፍፁም..!” የሚል እንደሆነ እንጠብቃለን!
ታዲያ ምነው ለነዚያ ግልፅ መለኮታዊ መመሪያዎች እጅ መስጠት
ተሳናችሁ?!
2- አላህ ስለ ቁርኣን ወደ እውነት የሚመራ ብርሃን፣ የተብራሩ
አንቀፆችን ያዘለ፤ ለግንዛቤ የቀለለ፤ በግልጽ ዐረብኛ ቋንቋ የወረደ
እና የመሳሰሉት መገለጫዎችን የተላበሰ እንደሆነ የሚነግረን ሁሉ
እውነት አይደለም ማለት ነው?!
መቼም “እውነት ነው እንጂ!..” ማለታችሁ አይቀርም! ታዲያ፦
2.1- የጌታን ህልውና በሚመለከተው በዚህ ታላቅ መሠረት
ላይ ቁርኣን የሚያንፀባርቀው ጉልህ መልዕክት ክህደትን
የሚያስገነዝብ ሊሆን ይችላል?!(2) 2.2- ወይስ አላህ በተዟዟረ ዘይቤ ራሱን ለማወደስ በቀጥታ
ጉድለትን የሚያስተላልፉ ገለፃዎችን ደጋግሞ ያሰፍራል?
2.3- እንዴትስ የቁርኣን አንቀፆች እርስ በርስ የሚቃረኑ
ግልፅና ድብቅ መልዕክቶችን አጣምረው ያስተላልፋሉ? እንዲያ
ከሆነ ቁርኣን ሰምና ወርቁ ከሚያደናግር የቅኔ ፈተና የባሰ
እንቆቅልሽ ነው ማለት አይደል?!

3- በዚህ ጉዳይ ላይ ሰዎች ምራቻን የሚያገኙት እናንተ
በምትዳክሩበት “አእምሯዊ” መንገድ ከሆነ ቁርኣን የመውረዱ
ፋይዳ ምንድነው?
3.1- እንዲያውም እንደናንተ አባባል ቁርኣን ብዙ ቦታዎች
ላይ ስለ አላህ መገለጫዎች የሚያንፀባርቀው ጉድለትን ስለሆነ
አማኞች እነዚህን ገለፃዎች ተከትለው በገፍ “ከሚጠሙ”
ጭራሹኑ ባይወርድ አይሻልም ነበር?!
3.2- ወይስ ዓላማው በውስጡ ያሉትን የአላህ መገለጫዎች
በግሪክ ፈላስፋዎች መርሆ መሠረት እንደምንም ማፋረስና
መልዕክታቸውን በተገኘው መሳሪያ መቆልመም የሚችለው
“ጮሌ” ማን እንደሆነ እድሜ በማይፈታው የእንቆቅልሽ
ፈተና መለየት ነው?!
3.3- ውዝግባችንን ሁሉ ወደ አላህና መልዕክተኛው
አስተምህሮት እንድንመልስ በቁርኣን ውስጥ በአፅኖት
የታዘዝነውስ “እንቆቅልሹን” ይባስ ለማወሳሰብ ነው?!
አንዳንዶች ከነዚህ ፅኑ ጥያቄዎች ለመገላገል የሚመዙት አንድ
ደካማ መልስ አለ፦ «እነዚህን አንቀፆች ያወረደው ሊፈትነን
ነው!» ይላሉ!
ይህ በዚህ ቦታ በፍፁም የማይገጥም መልስ ነው፤ ምክንያቱም፦
ሀ- አላህ ሰዎችን የሚፈትነው እውነቱን ከጥመቱ በግልፅ የሚለዩ
መመሪያዎችን ካወረደ በኋላ ብቻ ነውና! አላህ እንዲህ ብሏል፦
 «አላህ ህዝቦችን ከመራቸው በኋላ የሚጠነቀቁትን ግልፅ
እስኪያደርግላቸው ድረስ የሚያጠማቸው አይደለም!» [አት-ተውባህ 115]
በነዚህ ሰዎች ግንዛቤ መሰረት ግን እርሱ አምሳያ እንደሌለው
በደፈናው ከሚጠቁሙ ጥቂት አንቀፆች በቀር ባህሪያቱ በዝርዝር
የተወሱባቸው አንቀፆችን ጉልህ መልዕክት መቀበል እንደማይገባ
በቁርኣንም ይሁን በመልዕክተኛው አንደበት አንድም ግልፅ መረጃ
ሳያስተላልፍልን የራሱን ቃል ተከትለን መንገድ ከሳትን በኋላ
ለቅጣት ሊዳርገን ነው ማለት ነው!
ለ- ይህ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እጅግ ያመዘነና አብዛኛውን አማኝ
ለጥመት የሚዳርግ ፈተና ይሆን ነበር፦ ለመሆኑ እነኚህን ግልፅ
መልዕክት ያዘሉ አንቀፆችና ነብያዊ አስተምህሮቶች በ“ዒልመ’ል-
ከላም” መርሆዎች ገልብጠው መረዳት የሚችሉት “ሙስሊሞች”
ስንት ናቸው?!
ሐ- ይህ ከላይ እንደተብራራው የቁርኣንና የሐዲሥ አስተምህሮት
ግልፅነትን የሚቃረን አባባል ነው!
መ- ይህ በቁርኣንና በሐዲሥ የተወደሱት ቀደምት ትውልዶች
የማያውቁት አዲስ ፍልስፍና ነው፤ እውነት ቢሆን ከሌሎች በፊት
አውቀውት ለተከታዩ ትውልድ በገለፁት ነበር።
ሌሎች ምክንያቶችንም መጥቀስ ይቻላል..
4- የአላህ መልዕተኛ (صلى الله عليه وسلم (ዘንድ ኢስላምን ለመማር አዋቂውም
አላዋቂውም፣ ከተሜውም አገሬውም፣ ትልቁም ትንሹም ሁሉም
ከተለያየ የግንዛቤ ደረጃቸው ጋር ሲመጡ እርሳቸው አንዱን
ከሌላው ሳይለዩ የአላህን ባህሪያት ያዘሉትን ቁርኣናዊ አንቀፆችና
ነብያዊ አስተምህሮቶች ያለ “ማስጠንቀቂያ” በገሀድ ያስተላልፉ
ነበር። ታዲያ፦
4.1- ግልፅ መልዕክቶቻቸው የተፈለጉ ባይሆን ኖሮ
የ“ተእዊል” ማብራሪያዎችን በማከል ተከታዮቻቸውን
ከውዥንብር እንዳያድኑ ምን ከለከላቸው?!
4.2- እንዴትስ ሙዐጥ-ጢላዎች ዘውትር እንደሚያደርጉት
ባህሪያቱን በግልፅ ባያፋርሱ እንኳ ቢያንስ አንድ ቀን እንኳ
ቀጭን ጥቆማ ሳያስተላልፉ አለፉ?
5- በአላህና በመልዕክተኛው አንደበት የተወደሱት ሰሓቦችና
ተከታይ ትውልዶች የሙስሊሙ ህብረተሰብ ቀዳሚ ተምሳሌትና
አርዓያ መሆናቸው ይታወቃል። ታዲያ፦
5.1- ይህን መሠረታዊ “እውነታ” እነኚህ ምርጥ ትውልዶች
ሳይረዱት ቀርተው ከጊዜ በኋላ የመጡት የከሃዲያን ፍልስፍና
አቀንቃኞችና የእምነት ኋላ ቀሮች ደረሱበት ማለት ነው?!
5.2- ወይስ ሰለፎች እናንተ እንደምታደርጉት አጋጣሚ
ሲመቻችም ሳይመቻች የእነዚህን መረጃዎች መልዕክት ለማፋረስና ለመቆልመም ያልታደሉት ለዲን ‘እንደ እናንተ’
የሚቆረቆሩ ስላልነበሩ ነው?!
5.3- ይልቁንም በቁርኣንና በሐዲሥ የፀደቁትን የጌታ ባህሪያት
በቀጥታና በተዘዋዋሪ የሚያረጋግጡ ግልፅ ንግግሮችን ይሰነዝሩ
የነበረውስ ሆን ብለው ጉዳዩን ለማድበስበስ ነበር?!


---
#በመጨረሻም አላህ ራሱን የገለፀባቸውን ባህሪያት ማፋረስን እንደ
መሠረታዊ እምነት በመቁጠር በተለያዩ ውዥንብሮች የሙስሊሙን
ህብረተሰብ ሰላም ለሚያደፈርሱት ወገኖች የሚከተለውን ስጦታ
አበረክታለሁ፦

#ታሪካዊ.ውይይት

“ቁርኣን ፍጡር ነው!” የሚለውን የአላህን የመናገር ባህሪ
የሚያፋርስ የክህደት አቋም ባለመቀበላቸው ታስረው የነበሩ አንድ
በእድሜ ጠና ያሉ ዓሊም ከአሕመድ ኢብን አቢ ዱኣድ
(3) ጋር
ኸሊፋው አል-ዋሢቅ (232 ዓ.ሂ) ባለበት ያደረጉትን ምልልስ
በአጭሩ እንደሚከተለ
104 views15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-07 10:50:38 #የአማኞች ጋሻ
#ክፍል 58

#ሶስተኛ፦ አንቀፆቹ እርሱ በ‘ዛቱ’ ከእኛ ጋር ተቀላቅሎ መገኘቱን
ጭራሽ እንደማያስገነዝቡ ከሚያስረዱት እውነታዎች መካከል
አብዛኛዎቹ የእውቀቱን ፍፁምነትና መሰል መልዕክቶችን
በሚያረጋግጡ አገባቦች የታጀቡ መሆናቸው ነው።
ለምሳሌ የላይኛውን አንቀፅ በሙሉ አገባቡ እናጢነው፦
 «እርሱ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀናት የፈጠረ፤
ከዚያም በዐርሹ ላይ ከፍ ያለ ነው፤ በምድር ወስጥ የሚገባውን፣
ከርሷም የሚወጣውን፣ ከሰማይ የሚወርደውንም በእርሷ ውስጥ
የሚያርገውንም ያውቃል፤ እርሱም የትም ብትሆኑ ከናንተ ጋር
ነው፤ አላህም የምትሰሩትን ተመልካች ነው!»[አል-ሐዲድ 4]

ልብ ይበሉ! በዐርሹ ላይ መሆኑን ከገለፀ በኋላ የእውቀቱን
ፍፁምነት በምሳሌዎች አስገነዘበን፤ ከዚያም ከኛ ጋር መሆኑን ጠቅሶ
የምንሰራውን ሁሉ እንደሚመለከት በመንገር አንቀፁን ቋጨ።
ከፊትና ከኋላ ያሉት አረፍተ-ነገሮች የአብሮነት መልዕክቱ
በእውቀቱ፣ በማየቱና በመቆጣጠሩ የሚገለፅ መሆኑን ቁልጭ
አድርገው ስለሚያብራሩ የአንቀፁ ጉልህ መልዕክት ምን እንደሆነ
መረዳት አያዳግትም!
በዚህ ላይ ደግሞ ከዐርሹ በላይ መሆኑን በመክፈቻው ላይ አስቀድሞ
ማፅናቱ “ከናንተ ጋር ነው” ከሚለው ቃል እርሱ ራሱ በምድር
ከባሮቹ ጋር መሆኑን ለመገንዘብ ምንም ያህል መፈናፈኛ
አላስቀረም! አዎን! አላህ ከዐርሹ በላይ ከፍጥረተ-ዓለሙ ውጭ
ከመሆኑ ጋር ከዕውቀቱ የሚሰወር፣ ከእይታው የሚሸሸግ፣ ከቁጥጥሩ
የሚወጣ.. ቅንጣት ነገር ባለመኖሩ በትክክል ከባሮቹ ጋር ነው!
ስለሆነም በርካታ የሰለፍ ሊቃውንት ሁለቱን መልዕክቶች በአንድ
ላይ አያይዘው ይናገሩ ነበር። ለአብነት ያህል፦
 ታላቁ ሰሓቢይ ዐብዱ’ላህ ኢብኑ መስዑድ ( ) እንዲህ
ይላሉ፦
«..አላህም ከዐርሹ በላይ ነው፤ ከምትሰሩትም ምንም ነገር
አይሸሸግበትም!»
(1)
ሌላ ምሳሌ፦
 «አላህ በሰማያት ውስጥ ያለውን በምድርም ውሰጥ ያለውን
ሁሉ የሚያውቅ መሆኑን አታይምን? ከሦስት ሰዎች መንሾካሾክ
አይኖርም - እርሱ አራተኛቸው ቢሆን እንጂ፤ ከአምስትም
(አይኖርም) - እርሱ ስድስተኛቸው ቢሆን እንጂ፤ ከዚያ ያነሰም
የበዛም (አይኖርም) - እርሱ የትም ቢሆኑ ከነርሱ ጋር ቢሆን
እንጂ! ከዚያም በትንሣኤ ቀን የሠሩትን ሁሉ ይነግራቸዋል፤ አላህ
ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡»
[አል-ሙጃደላህ 7]

የአንቀፁ መክፈቻ ስለ እውቀቱ፣ መዝጊያውም ስለ እውቀቱ
እንደሚያወሳ ያስተውሉ! አዎን! ቀደምት አበው መሰል አንቀፆችን
ተገን በማድረግ “አላህ ሁሉ ቦታ ነው” ሲሉ ለሚከራርከሩ ወገኖች
ማምታቻ ይህን መሰል ማብራሪያ እንደ እርማት ይሰጡ ነበር። (2 )
አሁንም ሌላ ምሳሌ፦
 «(አላህም) “አትፍሩ! እኔ ከናንተ ጋር ነኝና - እሰማለሁ
አያለሁም!” አለ።»
[ጣሃ 46]
አራተኛ፦ አላህ ከፍጡራኑ በላይ መሆኑ ስፍር ቁጥር በሌላቸው
መረጃዎች የተረጋገጠ በመሆኑ አብሮነቱ ከባሮቹ ጋር በቦታ
መቀላቀሉን ሊያመላክት አይችልም!
(3)  በጥቅሉ ይህ የሰለፎች ግንዛቤ ከሁል ጊዜው መርሃቸው ያፈነገጠ
“ተእዊል” እንዳልሆነ ግልፅ ሆኗል፤ ምክንያቱም አላህ ከፍጡራኑ
ጋር መሆኑን የገለፀባቸው ማስረጃዎች ቀድሞውኑ የቦታን መጋራት
የሚያስገነዝቡ ስላልሆኑ መልዕክታቸውን ከላይ በተገለፀው መልኩ
ማፅደቁ ጉልህ ቋንቋዊ ይዘታቸውን መከተል እንጂ የ“ተእዊል”
ትርጓሜን ማራመድ አይደለምና! ይህንን የግድ “ተእዊል” ብለን
መጥራት እንዳለብን የሙጥኝ ብሎ የሚሞግት ካልለ ደግሞ፦ ይህ
ተፍሲር የተዕጢል አራማጆች እንደሚያደርጉት የማያወላዱ
ማስረጃዎችን በሚፃረር ፀጉር ስንጠቃ ቃላትን መጠምዘዝና ትርጉም
ማዛባት ሳይሆን ቁልጭ ያሉ ማስረጃዎችን ተመርኩዞ እውነታውን ማብራራት ነው! ስለዚህ በምንም መልኩ የሐቅ ባለቤቶች መንገድ
ከጥመት ሰለባዎች መንገድ ጋር ሊነፃፀር አይችልም። አል-ሐምዱ
ሊ’ላህ!
ከላይ በተብራራው መልኩ አላህ ቅርብ መሆኑን የጠቀሰባቸውና
መሰል ገለፃዎች ላይ የሚነሱ ተመሳሳይ ውዥንብሮችም መልስ
ሊያገኙ ይችላሉ!




(1) “አል-ሙዕጀሙ’ል-ከቢር” ሊ’ጥ-ጠበራኒ (9/228)፣ “አር-ረድ-ዱ ዐለ’ል-
ጀህሚይ-ያህ” ሊ’ድ-ዳሪሚይ ገፅ 55፣ “አት-ተውሒድ” ሊብኒ ኹዘይማህ
(1/243-244)፣ “አል-ዐዞማህ” ሊአቢ’ሽ-ሸይኽ (2/565)፣
“ሸርሑኡሱሊ’ዕቲቃዲ አህሊ’ስ-ሱን-ናህ” ሊ’ል-ላለካኢይ (3/395-396)፣
“አል-አስማኡ ወስ-ሲፋት” ሊ’ል-በይሀቂይ (2/291) ..እና በሌሎች
መዛግብት የተላለፈ ሲሆን አል-ኢማም አዝ-ዘሀቢይ [“አል-ዑሉው” ገፅ
79] እና ሌሎች የዘገባውን ትክክለኝነት መስክረዋል።

(2) ለተወሰኑ ጥቅሶች “አል-አሣሩ’ል-መርዊይ-ያህ ፊ ሲፈቲ’ል-መዒይ-ያህ”
የተሰኘውን መፅሀፍ ከገፅ 18 ጀምሮ ይመልከቱ!


(3) የአላህን ከፍጥረተ-ዓለሙ በላይ መሆን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ
የሚያረጋግጡ ዝርዝር መረጃዎች ከሺህ እንደሚበልጡ አንዳንድ ቀደምት
ምሁራን ተናግረዋል! ለምሳሌ ከአንጋፋዎቹ የሻፊዒያህ መዝሀብ ሊቃውንት
አንዱ እንዲህ ይላሉ፦ «በቁርኣን ውስጥ አላህ ከፍጥረታቱ በላይ እንዳለ
የሚያመለክቱ አንድ ሺህ ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ መረጃዎች አሉ!»
(“መጅሙዑ’ል-ፈታዋ” ጥራዝ 5 ገፅ 121 ይመልከቱ።) በርካታ የኢስላም
ሊቃውንትም የተወሰኑት መረጃዎችን ያሰባሰቡ ጥራዞችን ደርሰዋል!



http://t.me/sadamnassirr
96 views07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-05 17:14:25 ሎችንም የተውሒድ ዕውቀት ለመሠብሠብ join


በ telegram

t.me/sadamnassirr s.

በ FB
https://www.facebook.com/100041066853907/posts/146476536731241/?app=fbl
1.0K views14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-05 17:14:25 #የአማኞች ጋሻ
#ክፍል 57


#“እናንተም.እንደኛው..!”

ሙዐጥ-ጢላዎች የሚያራምዱት የ‘ተእዊል’ ቀመር ከመሠረቱ
የተፋለሰ እንደሆነ አይተናል!
በዚህም የተነሳ የነብያት ተከታዮች ከቋንቋዊ አገባብ አንፃር ጎልቶ
የሚንፀባረቀውን መልዕክት የሚያፀድቁባቸውን አንዳንድ ቀጥተኛ
ትርጓሜዎች እንደ “ተእዊል” ቆጥረው “የኛም ‘ተእዊል’ እንደዚህ
ነው!” በማለት የራሳቸውን ጥመት ለማቃናት ይሞክራሉ!
 የዚህ ውዥንብር ዋነኛ መነሻ ከላይ እንደተጠቆመው የአንድን
ንግግር መልዕክት ጉልህነት የሚያዩት ከተሳሳተ አቅጣጫ መሆኑ
ነው!

ምሳሌ
ከዚህ በመነሳት የ“ተዕጢል” አራማጆች የሐቅ ባለቤቶችን
ከሚሞግቱባቸው ምሳሌዎች አንዱን እንመልከት፦
- አላህ እንዲህ ብሏል፦
 «እርሱም የትም ብትሆኑ ከናንተ ጋር ነው!»[አል-ሐዲድ 4]

#ብዥታ

ይህንና መሰል አንቀፆችን በማጣቀስ የሐቅ ተከታዮችን እንዲህ ሲሉ
ይሞግታሉ፦ «የነዚህ አንቀፆች ‘ጉልህ’ መልዕክት የሚያስገነዝበው
አላህ በምድር ላይ ከሰዎች ጋር ተቀላቅሎ እንዳለ ነው! ሆኖም
በእውቀቱ፣ በመስማቱ፣ በማየቱ፣ በቁጥጥሩ ..ወዘተ እንጂ እርሱ
ራሱ በ‘ዛቱ’ ከኛ ጋር እንዳልሆነ ማመናችሁ ወደ “ተእዊል”
እንዳመራችሁ የሚያሳይ ነው! ስለዚህ እናንተ ጉልህ መልዕክቱን
እንዳለ መቀበል ስለማይቻል ይህን “ተእዊል” እንደፈፀማችሁት
እኛም ጉልህ መልዕቶችን መቀበል በማይቻልበት ቦታ ላይ
ተእዊልን እንፈፅማለን!»

#መልስ
ይህ ውዥንብር ውድቅ እንደሆነ ከሚያረጋግጡ በርካታ ምላሾች
መካከል ጥቂቱን እነሆ፦

#አንደኛ፦ ቀድሞውኑ የነዚህ አንቀፆች ጉልህ መልዕክት እናንተ
እንዳላችሁት አላህ በ‘ዛቱ’ ምድር ላይ ከባሮቹ ጋር ተቅላቅሎ
እንዳለ የሚያስገነዝብ ሊሆን አይችልም፤ አብዛኛዎቹ ሙስሊሞችም
አንቀፆቹን ሲሰሙ ይህ አፀያፊ እሳቤ በአእምሯቸው ጭራሽ ውል
የማይል ሆኖ ሳለ እንዴት ‘ጉልህ’ ይባላል?! በኢስላም ታሪክም
አንድም ዓሊም መሰል አንቀፆችን እናንተ በምትወጥኑት መልኩ
አልተረዳም! ይልቁንም አብሮነቱ በእውቀቱ፣ በመስማቱ፣
በማየቱ፣ በመቆጣጠሩና በመሳሰሉት ይዘቶች እደሆነና እርሱ ራሱ
ግን ከዐርሹ በላይ እንደሆነ ያለ ምንም ውዝግብ ተስማምተዋል!
ይህንን ስምምነታቸውን ከዘገቡት በርካታ ሊቃውንት መካከል አንዱ የሆኑት አል-ኢማም አቡ ዑመር አጥ-ጠለመንኪ (429 ዓ.ሂ)
እንዲህ ይላሉ፦
«የሱን-ናህ ተከታይ ሙስሊሞች ژ እርሱም የትም ብትሆኑ ከናንተ
ጋር ነው! ژ የሚለውና መሰል የቁርኣን መልእክት ‘እውቀቱ’
እንደተፈለገበትና አላህ ራሱ ደግሞ ከሰማያት በላይ በዐርሹ ላይ
በሻው ሁኔታ ከፍ ብሎ እንዳለ ተስማምተዋል!»
(1)
ሌሎች ሊቃውንትም ይህንን የሰለፎች ስምምነት አፅድቀዋል።(2)
ይህ እውነታ አንቀፆቹ የሚያንፀባርቁት ጉልህ መልዕክት እናንተ
የምትሉት አይነት ሊሆን እንደማይችል ያረጋግጣል!

#ሁለተኛ፦ “ከናንተ ጋር” (معكم (የሚለው አገላለፅ በዐረብኛም
ይሁን በሌሎች ቋንቋዎች የሚያስተላልፈው መሠረታዊ መልዕክት
ሰፊ በመሆኑ ጥቅል አብሮነትን እንጂ የግድ የቦታ መጋራትን የሚያስገነዝብ አይደለም! ይህንን ጥቅል መሠረታዊ መልዕክት
በተወሰነ ይዘት ላይ የሚገድበው ቃሉ የተነገረበት አገባብና አኳያ
ነው። ‘ጉልህ’ መልዕክት የሚባለውም ከዚህ አንፃር ሰዎች በቀላሉ
የሚገነዘቡት መልዕክት ነው።
ለምሳሌ፦ በጎም ይሁን መጥፎ ተግባርን ከሌሎች ጋር መጋራት በአብሮነ معية ሊወሳ ይችላል፤ አላህ እንዲህ ብሏል፦

 «እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን (በመፍራት) ተጠንቀቁት፤
ከእውነተኞችም ጋር ሁኑ!»[አት-ተውባህ 119]
እንዲሁም መላኢካዎች ለመርየም እንዲህ እንዳሏት ነግሮናል፦
 «..ከአጎንባሾች ጋርም አጎንብሺ (ስገጂ)!»[አሊ ዒምራን 43]
ይህ መቼም እርሷ ከወንዶች ጋር ተቀላቅላ እንደምትሰግድ
አያመላክትም!
- እንዲሁም አንድ ሰው በአንድ ሀይማኖታዊ ወይም ሌላ ርዕስ ላይ
ስላለው አቋም ሲጠየቅ “ከ‘እገሌ’ ጋር ነኝ!” ብሎ ሊመልስ
ይችላል፤ ምናልባት ግን በእሱና በ‘እገሌ’ መካከል ሰፊ የቦታ ርቀት
ይኖራል፤ እንዲያውም ‘እገሌ’ ከብዙ ክፍለ-ዘመናት በፊት የኖረ ግለሰብም ሊሆን ይችላል! ስለዚህ ከዚህ አገባብ የምንረዳው ጉልህ
መልዕክት በአቋም ከርሱ ጋር መሆኑን እንጂ አንድ ቦታ ላይ
መሰባሰባቸውን አይደለም!
- እንደዚሁ ሁሉ “በንግድ ስራ ከእገሌ ጋር መሆን፣ በጋብቻ
ከእገሌ ጋር መሆን፣ በሀሳብ ከእገሌ ጋር መሆን፣ በቦታ ከእገሌ ጋር
መሆን..” የሚሉት አባባሎች በአገባባቸው ልዩነት የተነሳ የተለያዩ
የአብሮነት መልዕክቶችን ያስጨብጣሉ!
- እንዲሁም ዐረቦች “ለሊቱን ሙሉ ስንጓዝ ጨረቃ ከኛ ጋር
ነበረች!” ሲሉ ከገለፃው ከጨረቃ ጋር በአንድ ቦታ መሰባሰባቸውን
የሚገነዘብ የለም! ምናልባትም አንድ ሰው “ይህ ጉልህ መልዕክቱ
ነው!” ብሎ ቢናገር ሊሳቅበት ይችላል!
- እንዲሁም በሌላ አገር ያሉ ሰዎችን በስልክ እያናገረ ወይም
በቀጥታ የምስል ቀረፃ ድርጊታቸውን እየተከታተለ ያለ ግለሰብ
“ከነእገሌ ጋር ነኝ..” ብሎ መናገሩ የተለመደ ነው።
- እንደዚሁም አንድ ንጉስ ወይም ባለ ፀጋ ወይም ሌላ ሰው በሌላ
አገር ያሉ ወገኖቹን የተለያዩ እርዳታዎችን እንደሚለግሳቸው
ለመግለፅ “አይዟችሁ! እኔ ከናንተ ጋር ነኝ!” ይላቸዋል!
 አል-ኢማም አቡ ሐኒፋ አላህ በሰማይ (ከፍጡራኑ በላይ) እንጂ
በምድር አለመሆኑን በፅሁፍ ባሰፈሩ ጊዜ አንድ ሰው (وهومعكم)
(እርሱም ከናንተ ጋር ነው!) ስለሚለው አንቀፅ ሲጠይቃቸው
«ወደ አንድ ሰው ከርሱ የራቅክ ሆነህ ሳለ “እኔ ካንተ ጋር ነኝ!”
ብለህ እንደምትፅፈው ነው!» ብለው መመለሳቸው ተዘግቧል።
(3)
ስለዚህ በነዚህና በመሰል አኳያዎች ፍጡራን ሩቅ ካሉት ጋር
(አብረው) መሆናቸው የሚቻል ከሆነ አላህ ከፍጥረተ-ዓለሙ በላይ
ከፍ ያለ ሆኖ ከባሮቹ ጋር መሆኑ እንዴት ይታበላል?! የፍጡራን
አብሮነት የግድ በቦታ መሰባሰብን የሚያመላክት ካልሆነ የታላቁ
ፈጣሪ አብሮነት እንዴት ይህንን ያመላክታል?!
 አላህ ከባሮቹ ጋር መሆኑን የገለፃባቸው አንቀፆች በቋንቋዊ
አከሻሸናቸው ሁለት አይነት የአብሮነት መልዕክትን ሊያስገነዝቡ
ይችላሉ፦
1- ከሙስሊሙም ይሁን ከሌላው ጋር መሆኑን በሚያሳዩ አገባቦች
ላይ በእውቀቱ፣ በመስማቱ፣ በማየቱ፣ በቁጥጥሩ.. ወዘተ ከሁሉም
ጋር መሆኑን፤
2- አብሮነቱን በአማኞች ላይ በሚገድብ አገባብ ደግሞ ከላይኛው
መልዕክት ባሻገር በእርዳታው፣ በእንክብካቤው፣ በጥበቃውና
በመሳሰሉት አኳያዎች ከነርሱ ጋር መሆኑን።
እናም ከአንቀፆቹ በቀጥታ የምንረዳው ጉልህ መልዕክት ይህ
በመሆኑ የ‘ተእዊል’ ጥምዘዛ አያስፈልገውም!


t.me/sadamnassirr s.
(1) “አል-ዉሱል ኢላ መዕሪፈቲ’ል-ኡሱል” በሚለው መፅሀፋቸው ያሰፈሩት።
[“በያን ተልቢሲ’ል-ጀህሚይ-ያህ” (1/186)፤ “አል-ዑሉው” ገፅ 246
ይመልከቱ።]

(2) ከሰሓቦች ዘመን ጀምሮ የነበሩ ቀደምት ምሁራን የአላህ አብሮነት በእውቀቱና
በመሳሰሉት ይዘቶች እንጂ በ‘ዛቱ’ እንዳልሆነ የተናግሯቸውን አንዳንድ
ጥቅሶች ከአንቀፆቹ ማብራሪያዎች ጋር ለማየት “አል-አሣሩ’ል-መርዊይ-ያህ
ፊ ሲፈቲ’ል-መዒይ-ያህ” የተሰኘውን መፅሀፍ ይመልከቱ!

(3) “አል-አስማኡ ወስ-ሲፋት” ሊ’ል-በይሀቂይ (2/337) ይመልከቱ።



ኢንሻኣላሁወተላህ ይቀጥላል
በተወዳጅ የሱና ኡስታዞቻችን የተፃፉ መፅሐፎች ለማግኘት፡፡

1.2K views14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-01 16:40:23 የአማኞች ጋሻ 2ኛ ከለር እትም

ስለ አስማዕ ወሲፋት ጠቃሚ መርሆዎችን የሚያብራራ የሚነዙ ብዥታዎችንም በመረጃ የሚመልስ ጠቃሚ መፅሐፍ

@ustazilyas
12 views13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2019-12-01 15:53:56 #ክፍል 56
#የአማኞች ጋሻ

 «ያ ንግስና በእጁ የሆነው ጌታ ትሩፋቱ በዛ..»[አል-ሙልክ 1]

 «ያ የሁሉም ነገር ስልጣን በእጁ የሆነው (ጌታ) ጥራት
የተገባው ነው!»[ያሲን 83]

 «..መልካሙ (ሁሉ) በእጅህ ነው.።»
[ኣሊ ዒምራን 26]

እነዚህና መሰል አንቀፆች አላህ የንግስና፣ የስልጣንና የመልካም
ነገር ሁሉ ባለቤት መሆኑን ሲያስገነዝቡ እጅ እንዳለውም በዚያው
ያመላክታሉ፤ በመሠረቱ የእጅ ባለቤት ባይሆን ኖሮ እነዚህን መሰል
ገለፃዎች አያሰፍርም ነበርና!
በዚህ መሠረት አንዳንድ ጊዜ ቀደምት የኢስላም ሊቃውንት
እነኚህን መሰል አንቀፆች ሲያብራሩ የሐረጉን ጥቅል መልዕክት
ብቻ አስፍረው ማለፋቸው እንደ ‘ተእዊል’ የሚቆጠር አይደለም፤
የእጅ ባለቤት መሆኑ የታወቀ በመሆኑ በየቦታው መጠቀሱ የግድ
አይደለምና!
 በጥቅሉ የ‘ተእዊል’ አራማጆች ላለመስጠም ባገኘው እንጨት
ላይ እንደሚንጠላጠል ሰው ብዙ ቢፍጨረጨሩም ይህንን ማጣሪያ
ለማለፍ የሚያስችል መረጃ የላቸውም!
 አሁን ደግሞ ወደ አራተኛው ማጣሪያ እንለፍ፦ የአንቀፁን
ጉልህ መልዕክት ከለቀቁ ወዲህ ከ‘ዘይቤያዊ’ ትርጓሜዎቹ
አንደኛውን ለይቶ ለመምረጥ የሚያስችል በቂ ምክንያት
አያቀርቡም! እንዲያውም አብዛኛዎቹ በዚህም ይሁን በሌሎች
ቦታዎች ላይ ‘ተእዊላቸውን’ የሚያራምዱት በጥርጣሬ መንፈስ
“የተፈለገው እንዲህ ሊሆን ይችላል፣ እንዲያም ሊሆን
ይችላል..!” እያሉ የ‘ምናልባት’ ሀተታዎችን በመደርደር ነው።
 አል-ኢማም አድ-ዳሪሚይ (280 ዓ.ሂ) ለአንድ የጀህሚይ-ያህ
አቀንቃኝ ይህንን ብለዋል፦

«ተውሒድ ላይ ከትክክለኛው አንድ እምነት በቀር ተቀባይነትን
ሊያገኝ የሚችል እንደሌለ በመፅሀፍህ ጠቅሰህ የለ?! ታዲያ
እንዴት ትክክል መሆንህን ወይም መሳሳትህን በማታውቅበት
ንግግር ስለርሱ ትዘላብዳለህ?! ምክንያቱም ስለ ተውሒድ
አብዛኛውን ጊዜ በግምት ስትተነትን ነው የምናይህ! ግምት ደግሞ
ሊሳሳት ወይም እውነትን ሊገጥም ይችላል፤ ይህም “ተፍሲሩ
እንዲህ ሊሆን ይችላል፤ ይህን ያህል ተፍሲሮችን ያስተናግዳል፤
በባህሪያቱም የተፈለገው እንዲህ ሊሆን ይችላል፤ ከዚህ የተለየ
መልዕክትም ያስተናግዳል፤ ንግግሩም እንዲህ ያለ ትርጓሜ ሊኖረው
ይችላል..” የምትለው ንግግርህ ነው! “ሊሆን ይችላል” የሚለው
ግምት ሰዎች ሁሉ ዘንድ ጥርጣሬ እንጂ እርግጠኝነት አይደለም!
ግልፅ ያልሆነ የግል አስተያየት ነው! ከባህሪያቱ በአንዱ ላይ ብቻ
የተለያዩና ብዙ አይነት መላምቶችን “ሊሆን ይችላል” በማለት
የምትሰነዝር እንጂ ትክክለኛውን ለይተህ የምትመርጥ እንኳ አይደለህም! ታዲያ አንተ ራስህ ባህሪያቱን ሳታውቃቸው
እየባዘንክና ራስህ እርግጠኛ ባልሆንክበት መመዘኛ እያነፃፀርካቸው
እንዴት ሰዎችን ወደ ትክክለኛው ተውሒድ ልትጠራ
ትችላለህ?!»
(1) በመሠረቱ በዋነኝነት የሚያሳስባቸው ከጉልህ መልዕክቱ ማምለጥ
እንጂ የተፈለገውን አምላካዊ መልዕክት መረዳት እንዳልሆነ ከላይ
አይተናል!
 አምስተኛው ማጣሪያ ላይ ደግሞ ጭራሽ መፈናፈኛ የለም!
አላህ ለርሱ ልቅና የተገቡ እጆች እንዳሉት በማያወላዳ ቃል
የሚያረጋግጡትን ሌሎች ማስረጃዎች በምን አቅም ነው ሊጋፈጡ
የሚችሉት! እስቲ ለአብነት ያህል በጣም ጥቂቱን እንተዋወስ!
አላህ እንዲህ ብሏል፦
 «አላህንም በሚገባው ልክ አላከበሩትም! - ምድር በመላ
በትንሳኤ ቀን ጭብጡ ሆና ሳለ፤ ሰማያትም በቀኙ የሚጠቀለሉ
ሆነው..!»[አዝ-ዙመር 67]
የአላህ መልዕክተኛም (صلى الله عليه وسلم (የአንቀጹን መልዕክት በአፅኖት
ሲያረጋግጡ ጣቶቻቸውን እየጨበጡና እየዘርጉ በማሳየት እንዲህ
አሉ፦
 «አላህ ሰማያቱንና ምድሮቹን በሁለት እጆቹ ይይዝና “እኔ አላህ
ነኝ! እኔ ነጉሱ ነኝ!” ይላል።»
(2)
እንዲሁም እንዲህ ብለዋል፦
 «ምድር የትንሳኤ እለት አንድ ሙልሙል (ዳቦ) ትሆናለች፤
አንዳችሁ ዳቦውን እያገላበጠ ለጉዞ እንደሚያሰናዳው ሃያሉ (ጌታ)
በእጁ አገላብጦ ለጀነት ባለቤቶች መስተንግዶነት ያሰናዳታል!»(3)
 «ፍትኸኞች አላህ ዘንድ በብርኃን መንበሮች ላይ ከአር-ረሕማን
በስተቀኝ በኩል ይሆናሉ፤ ሁለቱም እጆቹ ቀኝ ናቸው..»
(4)
 የአላህ እጆች በነዚህና በሌሎች የቁርኣንና የሐዲሥ ማስረጃዎች
እንዲሁም በሰሓቦችና በታቢዒዮች አንደበት ‘ተእዊል’ን
ሊያስተናግዱ በማይችሉ የተለያዩ አገባቦች ከመቶ ጊዜ በላይ(5)
ተደጋግመው ተጠቅሰዋል! ከመያዝ፣ ከመጠቅለል፣ ከመጨበጥ፣
ከመዘርጋት፣ ከጣቶች፣ ከቀኝነት እና ከሌሎች መገለጫዎች ጋር
ተወስተዋል! እነዚህ መረጃዎች የማያሳምኑት አላህ ልቦና
እንዲሰጠው ይማፀን!



“እናንተም እንደኛው..!”
ከሚለው ይቀጥላል join



(1) “ነቅዱ ዑሥማን ኢብኒ ሰዒድ ዐላ ቢሽር አል-መሪሲ አል-ዐኒድ” ሊ’ድ-
ዳሪሚይ (2/798-799)


(2) (የሙስሊም ዘገባ) አል-ቡኻሪ (7412)፣ ሙስሊም (2788)፣ ከኢብኑ ዑመር
እንዳስተላለፉት። እንዲሁም አል-ቡኻሪይ (7283) እና ሙስሊም (2787)
ከአቡ ሁረይራህ የዘገቡትን ተመሳሳይ ሐዲሥ ይመልከቱ!

(3) አል-ቡኻሪ (6520)፣ ሙስሊም (2792)፣ አቡ ሰዒድ አል-ኹድሪይ
ያስተላለፉት።


(4) ሙስሊም (1827)፣ ዐብዱ’ላህ ኢብኑ ዐምር ያስተላለፉት። እጆቹ ፍጡራን
ዘንድ እንደተለመደው የሚበላለጡ ሳይሆኑ ሁለቱም በትሩፋት ቀኝ ናቸው፤
ይህ የታወቀ የዐረብኛ ስልት ነው። ከዚህ አንፃር ሌላኛው እጁን በ‘ግራ’
መሰየም ምንም እንኳ አንዳንድ አወዛጋቢ መረጃዎች ላይ ቢፀድቅም አላህን
ከማላቅ አንፃር ቃሉን አለመጠቀሙ ተገቢ ስርዓት መሆኑን ያሳያል።


(5) “ሙኽተሰር አስ-ሰዋዒቅ አል-ሙርሰላህ” (3/984)






ኢንሻአላህ ይቀጥላል

በተወዳጅ የሱና ኡስታዞቻችን የተፃፉ መፅሐፎች ለማግኘት፡፡

ሌሎችንም የተውሒድ ዕውቀት ለመሠብሠብ join


በ telegram

t.me/sadamnassirr s.

በ FB
https://www.facebook.com/100041066853907/posts/146476536731241/?app=fbl
90 views12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ