Get Mystery Box with random crypto!

ሰኔ 01/2015 በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ዙሪያ ውይይት ተካሄደ። ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ | Bule Hora University

ሰኔ 01/2015
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።
ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መውሰድ አለባቸው በሚል ትምህርት ሚኒስተር ያወረደውን መመሪያ መሠረት በማድረግ እና ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊው ሥራዎች እየተሠሩ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡ስለሆነም እስከዛሬ በነበረው ሂደት አፈፃፀሙ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለመገምገም የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ እና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ከዩኒቨርሲቲው ኮሌጅ ዲኖች፣የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች እና ከየትምህርት ክፍሎች የተወከሉ የተማሪ ተጠሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ