2022-08-19 17:15:50
በብርሃን መመላለስ
የህይወቴ ብርሃን ኢየሱስ ነው። ስለዚህ በህይወት ለመኖር የሚያስፈልገኝ ኢየሱስን ማወቅ ብቻ ነው። ምክንያቱም ኢየሱስ የህይወት ሁሉም ነገር ነው። የህይወት ሁሉም ነገር በእርሱ ውስጥ አለ። በኢየሱስ ውስጥ የሌለ መልካም ነገር ፈፅሞ የለም።
መለኮት ኢየሱስን የጥያቄ ሁሉ ብቸኛ መልስ አድርጎ ያቀረበው ለዚህ ነው።
ይህ ብዙዎች በስሜትና በደመ ነፍስ በልማድም እንደሚያደርጉት የቃላት ጨዋታ አይደለም። ኢየሱስ ህይወት እንጂ የልማድ መዝሙርና ስብከት ማድመቅያ አይደለም። 1ዮሃ5:20
የእግዚአብሔር ቃልም እንድሁ ህይወት እንጂ የምንም ማሟያ አይደለም። ዝም ብሎ ለራስ በሚመች መልኩ ፈንድሻ እየዘሩ መቀለድ ትርፉ ተያይዞ መጥፋት ብቻ ነው።
ይህ እውነት የምር መገለጥን የሚፈልግ ነገር ነው። ይህን ማወቅ ደግሞ ህይወትን ለሚፈልግ ሁሉ ግዴታ ነው። ይህ እውነት ያልበራለት ሰው መቼም ህይወት የለውም። የመለኮት ሁሉም ነገር ያለውና የተገለጠው የሚገለጠውም በአየሱስ በኩል ብቻ ነው። ኢየሱስ የመለኮት ሁሉ በሁሉ ነው። ቆላ3:11
ለእኔ ኢየሱስ የህይወቴ ብርሃን ነው። በጨለማ መኖር የማልችለው መለኮት ራሱን የሁሉም ነገሩ መገለጥ በሆነው በልጁ ስለ ገለጠልኝ ነው። የተፈጠርኩለት ዓላማ ገብቶኛል። ሁሉም ነገር የሚለካው ከዚያ አንፃር ነው። የቅዱሳን አባቶችና እናቶች ሁሉ ምስጥር ይህንን መረዳት ነው።
የህይወት ብርሃን ኢየሱስ ብቻ ነው። ሌላው ነገር ተረትና ውሸት ብቻ ነው።
ይህ ብርሃን አንዴ የበራለት ሰው ለከንቱ ነገርና ለጨለማ(ለሞት) አይገኝም አይገዛምም። እኔ ለምንም ሌላ ነገር የማልገዛው ኢየሱስ አንዴ የልብ ዓይኔን በዚህ ምስጥር ስለ አበራው ነው። የቤት ስሜ ራሱ አበራ ነው።
ለእናንተም ይህ እንዲሆንላችሁ ምኞቴ ነው። ሁሌም በፀጋው የሚደክመውና የሚጋደለውም ለዚህ ነው።ህያው አምላክ የትውልድን የልብ ዓይን ለመክፈት ጠርቶናል። የእኔ የመንፈሳዊ ስኬቶቼ ሁሉ ምስጥር ይሄው ነው። በብዙ ነገር የሁሉም ታናሽ ቢሆንም ልዑል ግን የልቡን ምስጥረኛ አድርጎኛል።
ኢየሱስ የበራለት ሰው የራሱ የኢየሱስ እንጂ የሌላ የምንም ነገር ባርያ መሆን ፈፅሞ አይችልም። እውነትን(ኢየሱስን) ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል። ዮሃወ8:32፣ ዮሃ14:6 ማለት ይህ አይደል? ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ ያለው እርሱ ራሱ ነው።
ለጵላጦስ እውነትን ልመሰክር ስለዚህ ተወልጃለሁ ያለውም እርሱ ራሱ ነው። ዮሃወ18:37-38 አይገርምም ንጉስ ጵላጦስ ግን እንደ ዘመኑ ትውልድ እውነት ምንድን ነው? ብሎ ጠየቀው። መልሱ ራሱ ኢየሱስ ነበር።
ስለዚህ ይህ መለኮታዊ ምስጥር የበራለት ሰው እጅግ በጣም ብፁዕ ነው። ለሁሉም የሰው ዘር የሚያስፈልገውም ይህ ነው።
መንፈስ ቅዱስ ወደ ህይወታችን የመጣው በክርስቶስ ወዳለው የመለኮት እቅድና እውነት ልመራን ነው። ዮሃወ 14:17፣ 15:26፣ እና 16:13
መልእክቱን ለብዙ ሰዎች ሼር አድርጉት.....
ይቀጥላል......
@renal_sink
186 viewsGods good the all Time, 14:15