መንፈሳዊ ወጣትነት የሰው ልጅ በተለይ እኛ ወጣቶች የሚያጋጥሙን ፈተናዎች ሁሉም ግልጽ የሆነ መፍትሔ ላይገኝላቸው ይችላል። ፈተና ስንል የግድ የመከራና ችግር መፈራረቅ ብቻ ላይሆን ይችላል። ለምሳሌ ያሰቡት(ያቀዱትን) በዕለቱ እንዳንፈጽም የሚያደርግ ፈተና ፣ ምክንያቱ ያልታወቀ የጠባይ ለውጥ ፣ ወይም ደሞ የስሜት መለዋወጥን ብንመለከት ትናንት ወደድኩህ ከጎኔ አትራቅ ብለን የፍቅሩን ናፍቆት መጋፈጥን እንዳልፈራን ዛሬ ላይ ያ የቀድሞ ስሜታችን ጠፍቶ ይባስ ብሎ ለዐይናችንም እስክንጠየፈው የሚያደርሰን ዓይነት ፈተና ሁሉ ውሉ የማይጨበጥ የኛ የወጣቶች ፈተና ነው።
ስለዚህ ለእንደዚህ ዓይነት ፈተናዎችም ሆነ ኑሮን በስክነት ለመምራት መንፈሳዊነትን የመሰለ ጋሻ ፣ አማኝነትን የመሰለ ዋሻ የለም! ጋሻ ከተሰበቀ ጦር እንደሚከላከል ሁሉ መንፈሳዊነትም ከክፉ(ከማይጠቅም) ፈተና ይጠብቀናል ፤ ዋሻ ከዱር አውሬ ጥቃት የምናመልጥበት መጠለያ እንደሆነ ሁሉ አማኝነትም ከጠላት ክፉ ምክርና ሐሳብ መደበቂያ ባዕታችን ናት።
"የዘመኑ ኃላፊ ዘመናዊነት በፈረንጅ ኢ-አማኒነት ቢለካም እኛ ግን አማኞች በመሆን የማያልፈውን ዘመን እንዋጃልን! ምክንያቱም #ብርቱ_ወጣቶች ነን! " በርቱ! ለሐሳብ አስተያየትና ተሞክሮ ለማካፈል @productive_habeshaa እና @Tnx4Deshet
@bertuwetat
@bertuwetat