Get Mystery Box with random crypto!

መከላከያ ሰራዊት አሸባሪውን ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠውና እየደመሰሰው እንደሚገኝ | B B C News አማርኛ™

መከላከያ ሰራዊት አሸባሪውን ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠውና እየደመሰሰው እንደሚገኝ አስታወቀ!!

የአገር መከላከያ ሠራዊት ካለፈው የኅልውና ዘመቻዎች የጠላትን አሠላለፍ በውል በመገንዘብ አሸባሪውን የህወሓት ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠው እና እየደመሰሰው እንደሚገኝ አስታወቀ።

ሠራዊታችን የድል ሠራዊት ነው በሚል ባወጣው መግለጫ በየትኛውም ቦታና ጊዜ፣ አስቸጋሪ መልክአ ምድርንም ሆነ የአየር ፀባይ ተቋቁሞ ግዳጁን በድል አድራጊነት የሚወጣው ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ጠላትን በአስተማማኝ መመከት የሚችል ኃይል መሆኑን አረጋግጧል።

ሠራዊቱ ከራሱ ይልቅ ሕዝብን ያስቀደመ፣ ለሀገር እና ለሕዝብ ራሱን አሳልፎ የሠጠ ብሔራዊ ኩራታችን ነው ብሏል።

ጠላቶቻችን ሕዝባዊ ባህሪውን በውል ስለሚገነዘቡ ህፃናትንና ሴቶችን ከፊት አሰልፈው ክፍለ ዘመን ባለፈበት ጦርነት በሕዝብ መአበል መዋጋታቸው የሠራዊታችንን አይበገሬነትና ጀግንነት ጠንቅቀው ስለሚያውቁት እንደሆነ ገልጿል።ጠላት ለዜጎቹ ደንታ እንደሌለው ባሳየው በዚህ የኋላ ቀር ጦርነት ሠራዊታችን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና የኃላፊነት መንፈስ ግዳጁን እየተወጣ እንደሆነ በማመልከት አሸባሪው ህወሓት በለኮሠው እሳት መልሶ እየለበለበው እንደሚገኝ መከላከያ ሰራዊት አስታዉቋል።

@bbc_amharic1