በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ በሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች ከትናንት ጀምሮ በመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች እና ታጣቂዎች መካከል ግጭት እንደተቀሰቀሰ የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በግጭቱ የሰው ሕይወት እንደጠፋና ንብረቶች እንደወደሙ የዓይን ምስክሮች ተናግረዋል። ግጭቱ የተፈጠረው ከአጣዬ ከተማ ወጣ ብለው በሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች ነው። ወደ ገጠር ቀበሌዎች ገብቶ ከመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ጋር ግጭት ውስጥ የገባው የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እንደሆኑ የዓይን ምስክሮች ገልጸዋል። Via:- Wazema @bbc_amharic1 13.4K views16:47