2024-06-02 13:16:43
ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ
ቁጥር፡-096/24
አዋሽ ባንክ ለአዲስ አበባና አካባቢው ላሉት የባንኩ ቅርንጫፎችና ህንፃዎች በጥበቃ የስራ መደብ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
የምልመላ መስፈርቶች፡-
• የት/ደረጃ ፡- 8ኛ ክፍል ያጠናቀቀና ከዚያ በላይ
• የሥራ ልምድ ፡– በወታደርነት ሙያ ስልጠና የወሰደ ሆኖ በፖሊስ/መከላከያ ተቋም 2 (ሁለት) ዓመትና ከዚያ በላይ ያገለገለ፤
• ዕድሜ ፡- ከ25 – 60 ዓመት፣
• ከመከላከያ ወይም ከፖሊስ ተቋም በጡረታ ወይም በቀላል ጉዳት በቦርድ የተሰናበተ፤
• በጥበቃ ስራ በኮንትራትነት ለመቀጠር ፍላጎት ያለው እና በኮንትራት ባንኩ በሚመድበው ቦታ እና ሁኔታ ለመስራት ፈቃደኛ የሆነ፤
• የጤና ሁኔታ ፡- በአካልና በአዕምሮ ሙሉ ጤነኛ የሆነ፣ የአካል ብቃት ጥንካሬው ለጥበቃ ስራ ብቁ የሆነ፤ የሚሰጠውን የፅሁፍ፣ የቃልና የአካል ብቃት እንቀስቃሴ ፈተና ማለፍ የሚችል፤
• ደመወዝ፡- በባንኩ ስኬል መሰረት
• የቅጥር ሁኔታ፡– በኮንትራት
ማሳሰቢያ፣ አመልካቾች በእጅ የተፃፈ ማመልከቻችሁን እና ከላይ ከተገለፁት ማስረጃዎች በተጨማሪ ስርዝ ድልዝ የሌለበት የ8ኛ የሚኒስትሪ ሠርተፊኬት ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
በዚሁ መሠረት ከላይ የተገለፀውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ ቀናት የማስረጃችሁን የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በሚከተለው አድራሻ በመላክ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ማስታወቂያ የወጣበት ቀን:- ግንቦት 25 ቀን 2016 ዓ .ም
አዋሽ ባንክ
ቺፍ – ሂውማን ካፒታል ማኔጅመንት ኦፊሰር ኦፊስ
የፖ.ሳ.ቁ 12638
አዲስ አበባ
13.7K views10:16