Get Mystery Box with random crypto!

#ባል_አስይዞ_ቁማር ፡ ፡ #ክፍል_ሰላሳ_አራት ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ እቤት እንደገባች መ | አትሮኖስ

#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

እቤት እንደገባች መኝታ ቤቷን ዘጋችና ትንሽ እረፍት ልትወስድ ፈልጋ ጋደም አለች፡፡ነገ ቃልን እንደምታፈቅረው ልትነግረው በመወሰኗ በውስጧ የተፈጠረባት መረበሽን ተከትሎ ኃይለኛ እራስ ምታት እያንገላታት ነው..እራሷን ለሁለት ከፍሎ ይፈልጣት ጀመር .ከመኝታዋ እንደምንም እየተንገዳደገደች ተነስታ ኮመዲኖዋን ከፈተችና የህመም መስታገሻ መድሀኒት አወጣች ሁለት ፍሬ ወስዳ ወጠች.እንዲሁ መድሀኒቱ የህመም ማስታገሻ ይባላል እንጂ ድንዛዜ ውስጥ የሚከትና የሚያንሳፍፍ  ሀሺሽነት ባህሪ ያለው መድሀኒት ነው..ለአሷ ግን ይመቻታል፡፡መኝታዋ ላይ ተመቻችታ ተኛች፡፡ቀስ በቀስ ደስ የሚል ስሜት እየተሰማት መጣ..ደስ የሚሉ ሀሳቦች የአምሮዋን የፊተኛ ስፍረ መቆጣጠር ጀመሩ…እሷም በደስታ ፈቀደችላቸው..ድንገት የሆነ ቅፅበታዊ መገለጥ አይነት ነገር ሲከሰተ እየታወቃተ ነው...በአእምሮዋ የፊተኛው ሰሌዳ ላይ ብልጭ ድርግም...ብልጭ ድሮግም  ማለት የጀመረው ...አባቷን በአይኖቾ ያየችበት የመጨረሻ ቀን   ጓሮ ከትክልቶች መካለል ገብታ ተደብቃ ነበር..እንደዛ ያደረገችው የሚያማምር ቀለም ያላቸው አበቧች ቀልቧን ስለሳቧት ነበር...አበባ ትወዳለች...ማንም ሳያያት ሹክክ ብላ ገብታ ከየአይነቱ አንዳአንድ አበባ በመቀንጠስ ወደ ክፍሏ ይዛ በመሄድ በዛ እየተጫወቱ መደሰት ተደጋጋሚ ተግባሯ ነበር...የጊቢያቸውን አትክልተኛ የነበሩት አዛውንት ግን በስራዋ አይደሰቱም.. ሁሌ እንደተነጫነጩና ለእናቷ ስሞታ እንዳሰሙ ነበር...እናቷም ልታስቀይማቸው ስለማትፈልግ ፊታቸው ይቆጧትና ዞር ሲሉ ደግሞ የፍላጎቷን እንድታደርግ ያበረታቶት  ነበር...ይህ  የአበባ ፍቅሯ ዛሬም ድረስ ህያው ነው...ከመጨረሻ ጠላቷም ቢሆን የአበባ ስጦታ ከመቀበል ወደኃላ አትልም።

አዎ የመጨረሻዋ ቀን አሁን ጥርት ብሎ እየታያት ነው።ግን ውስጧ ከነበረ ለምንድነው እስከዛሬ ትዝ ሳይላት የቆየው ...?በየትኛው የአእምሮዋ ጎዳ ውስጥ ደብቃው ብትቆይ ነው?በጣም ያስገረማት ጉዳይ ነበር..በእለቱ ልክ እንደወትሯዋ እዛ የጓሮ  አበባ ውስጥ ተወሽቃ አባተዋና አያቷ ከውጭ  እየተጨቃጨቁ  መጡና እሷ ያለችበት አካባቢ ሲደርሱ ...ቆሙ።

"ከልጄ እንድትርቅ እፈልጋለሁ…. ሁሉን ነገር ጥለህ ይሄን ሀገር እንድትለቅና ዳግመኛም ተመልሰህ እንዳትመጣ አስጠነቅቅሀለሁ"አያተዋ ናቸው በቁጣ አበቷ ላይ የሚጮሁበት፡፡

"ምን እያሉ ነው ...ልጅ አለቺኝ ኦኮ...እንዲህ እንዲያደርጉኝ አልፈቅድም››አባቷ ነው ተቃውሞውን የሚያሰማው፡፡

"እሱን ከመስረቅህ በፊት ማሰብ ነበረብህ..."

‹ስርቆት› ምትለው ቃል በደማቅ ቀለም ነበር በእምሮዋ ላይ የፃፈችው፡፡

""በቃ አንዴ ተሳስቼያለሁ...ሁለተኛ አልደግምም...ከልጄ መለየት አልፈልግም"

"የልጅ ልጄ  በሌባ እጅ እንድታድግ አልፈልግም...ከአንተ ጋር አንድ ጊቢ ውስጥ ሆና በአንድ ከተማ አብሬህ መኖር አልፈልግም..አንድ ቀን ሰጥቼሀለሁ...ካለበለዚያ በማደርገው ነገር ታዝናለህ .."ብለውት ከዘራቸውን እየወዘወዙ ወደ ትልቁ ቤት ሲገብ ትዝ ይላታል።

አባቷ እዛው እቆመበት አካባቢ ያለ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ ልክ እሷ አሻንጉሊቶቾ ሲጠፍባት እንደምታደርገው እንባውን ሲያንጠባብ አይታለች...ከዛ ከተደበቀችበት ሹክክ ብላ ወጥታ ወደአባቷ ነበር ያመራችው...ተደብቃ የቀነጠሰችውን አበቦች ምንሞ ሳትሰስት እንዳለ ለአባቷ መስጠቷ ትዝ ይላታል። እሱም ጉያው ውስጥ ሸጉጦ በማቀፍ ጉንጮቾን  አንገቷን ትናንሽ እጆቾን እየቀያየረ እና እየደጋገመ ለሳዕታት ደክሞት እዛው ክንድ ላይ እስክተኛ ሲስማት እንደነበረ ትዝ ይላታል...ስለአባቷ  የተገለፀላት ትዝታ ይሄ ነው።ከእዛን ቀን በኃላ አላየችውም ...ከእንቅልፏ ስትነቃ እራሷን ያገኘችው መኝታ ቤቷ  ውስጥ በስርዓት ተኝታ  ነበር።ተነሳችና ‹ አባዬ› ብትል ለስራ ወጥቶል አሏት...በማግስቱ ብትጠይቅ ሩቅ መንገድ ሄዷል ተባለች...ጥያቄዋን ለወራት ብትደጋግምም ታገኝ የነበረው መልስ ግን በጣም አሰልቺ እና ተደጋጋሚ ነበር...ከዛ በህፃን አእምሮዋ አያቷ ላይ ቂም ያዘችበት...‹ሌባ ሌባ› የሚለው ከአያቷ አንደበት ወደ አባቷ የተሰነዘረው ቃል  በጨቅላ አእምሮዋ እየተመላለሰ  አስቸገራት ተሰቃየች? አዎ አሁን የዘመናት ችግሯ መነሻ ምክንያት ተገልፃላታል...በዛ የአባት ናፍቆት ያንገላታት በነበረበት ጨቅላ ዕድሜዋ እንደአባቷ መሆን በጣም መፈለጓ  ትዝ ይላታል፤ ...እንደ አባቷ ‹‹ሌባ..››ይሄንን ደግሞ ተግባራዊ ማድረግ የጀመረችው አባቷን ለመጀመሪያ ጊዜ ሌባ እያለ ሲያወግዘው የሰማችውን አያቷ በመስረቅና ለአባቷ በመበቀል ነው።

"የነገሮች እንዲህ መገጣጠምና መቆላለፍ በጣም  አስገራሚ ነው የሆነባት።ለዚህ ቃል ትልቅ ምስጋና ይገባዋል ፡፡መዳን ከፈለገች ወደ ልጅነት ጊዜዋ ተመልሳ ትዝታዎቾን እንድትቆፍር ባያሳስባት ..ምን አልባትም እኚ ነገሮች በውስጧ እንደተዳፈኑ እዛው ከስመው ይቀሩ ነበር...ግን አሁንም ያልገባት አባቷ ምን ቢሰርቅ ነው አያቷ እንደዛ ሊያስፈራሩት  የቻሉት..?ደግሞስ እንደ እሷ ልክፍት  ይዟት ካልሆነ የገንዘብ   ችግር እንደማይኖርበት እርግጠኛ ነች?ታዲያ ለምን?የእዚህ መልስ እናቷ ጋር ነው ያለው...ግን አሁን እሷ ያልገባት እሺ ለችግሯ መነሻ የሆነ ሰበበ ምክንያቱን አወቀች፡ ግን እንዴት ነው  ፈውስ እንዲሆናት ሊያግዛት የሚችለው?አልገባትም።ቢሆንም ደስ ብሏታል። ነገ ተነገ ወዲያ ደግሞ የሚገለፁላት  ከፈውሷ ጋር የተገናኙ ተጨማሪ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ። አዎ እናቷንና ቃልን  ማናገር እንዳለባት ወሰነች፡፡ ከዛ የሚሆነውን ለማየትድምዳሜ ላይ ደረሰች።
አይገርምም ግን የአንድ ቀን  ብጣቂ ገጠመኝ  የረጂሙ  የህይወታችንን  ጉዞ ላይ ጠንካራ ተፅእኖ ማሳረፍ ይችላል።አሁን ይሄን ታሪክ እንዲ አቆላልፍና አዋስቧ ሌላ ሰው ቢነግራት ስቃ ከማለፍ ውጭ እንደቁም ነገር ወስዳ ቦታ አትሰጠውም ነበር...አሁን ግን ዋጋ የከፈለችበት የራሷ ታሪክ ስለሆነ  ችላ ልትለው ፈፅሞ አትችልም። እናቷ ክፍል ገባች...ቁምሳጥናቸው አጠገብ ቁጭ ብለው በመስታወት እራሷቸውን እያዩ ፀጉሯቸውን እያበጠሩ ነበር፡፡በራፋን ከውስጥ ቆለፍችና ወንበር ይዛ ወደእሷቸው በመጠጋት  ከጎነናቸው ቁጭ አለች፡፡
"እማዬ አያቴና አባቴ በምን ጉዳይ ነበር የተጣሉት?"
እናቷ ጠያቄዋን እንደሰሙ ማበጠራቸውን አቁመው ፊታቸውን የሸፈነውን ፀጉሯቸውን ሰብስበው ወደኃላዋ ወረወሩና
‹‹  ምን አልሺኝ ?››አሏት በመኮሳተር
‹‹ ...አያቴ አባቴን ሌባ ነህ ብሎነው ከዚህ ቤት ያባረረው ...አባቴ ምን ሰርቆ ነው?››
"በሰማዕቱ ጊዬርጊስ ይሄን ጉድ ደግሞ ማነው የነገረሽ?
"ማንም አልነገረኝ እማዬ አስታውሼ ነው"
"አስታውሼ ማለት?"አይኖቾን አፍጥጣ፡፡
"አባዬ ከመጥፋቱ በፊት ከአያቴ ጋር ሲጨቃጨቁት ፊት ለፊት አበባ ውስጥ ተደብቄ ሰምቼያቸዋለሁ...አባቴ ከልጄ አይነጥሉኝ እያለ አባትሽን እያለቀሰ ሲለምን  ነበር..አያቴ ግን ከሌባ ጋር አንድ ቤትም አንድ ከተማም አብሬ አልኖርም..ሀገር ጥለህ ጥፋልኝ ሲለው በጆሮዬ ሰምቼለሁ?እና አባቴን ያባረራችሁት ብር ስለሠረቃችሁ ነው ወይስ ወርቅ?"