2022-04-02 01:02:59
የረመዷን ወር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥185 እንድትጦሙ የተጻፈባችሁ ያ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድ እና እውነትን ከውሸት ከሚለዩም ገላጮች አንቀጾች ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጡመው፡፡ شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ
"ሸህር" شَهْر የሚለው ቃል "ሸሀረ" شَهَرَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ወር" ማለት ነው፥ "ሸህር" شَهْر የሚለው ቃል በቁርኣን ውስጥ በነጠላ የመጣው 12 ጊዜ ነው። የሚያጅበው የወሮች ቁጥር አሏህ ዘንድ በአሏህ መጽሐፍ አሥራ ሁለት ነው፥ እነዚህም፦
1ኛው ወር "ሙሐረም" مُحَرَّم
2ኛው ወር "ሶፈር" صَفَر
3ኛው ወር "ረቢዑል-አወል" رَبِيع ٱلْأَوَّل
4ኛው ወር "ረቢዑ አስ-ሳኒይ" رَبِيع ٱلثَّانِي
5ኛው ወር "ጁማዱል-አወል" جُمَادَىٰ ٱلْأَوَّل
6ኛው ወር። ጀማዱ አስ-ሳኒይ" جُمَادَىٰ ٱلثَّانِي
7ኛው ወር "ረጀብ" رَجَب
8ኛው ወር "ሸዕባን" شَعْبَان
9ኛው ወር "ረመዷን" رَمَضَان
10ኛው ወር "ሸዋል" شَوَّال
11ኛው ወር "ዙል-ቀዕዳህ" ذُو ٱلْقَعْدَة
12ኛው ወር "ዙል-ሒጃህ" ذُو ٱلْحِجَّة ናቸው፦
9፥36 የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ ከእነርሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፡፡ إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65 ሐዲስ 4662
አቡበከር”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ”ዘመን አላህ ሰማያትን እና ምድር በፈጠረበት ቀን የቀድሞ ሁኔታ ይመለሳል። አንድ ዓመት ዐሥራ ሁለት ወር ነው፥ ከእነርሱም አራቱ የተከበሩ ናቸው። ሦስቱ ተከታታይ ዙል-ቀዒዳህ፣ ዙል-ሒጃህ፣ ሙሐረም ናቸው፥ አራተኛው በጀማዱ-ሣኒ እና በሻዕባን መካከል ያለው ረጀብ ነው። عَنْ أَبِي بَكْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ إِنَّ الزَّمَانَ قَدِ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ، السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا، أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ، ثَلاَثٌ مُتَوَالِيَاتٌ، ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ
“ረመዷን” رَمَضَان የሚለው ቃል "ረመዶ" رَمَضَ ማለትም "ደረቀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ድርቀት” ወይም “ሞቃት” ማለት ነው፥ ረመዷን የወር ስም እንጂ የጦም ስም አይደለም። የተቆጠሩ ቀኖች የያዘው ረመዷን 9ኛው ወር ሲሆን ይህ ወር የሚጦምበት ምክንያት ቁርኣን ከጥብቁ ሰሌዳ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ የወረደበት ወር ስለሆነ ነው፦
2፥185 እንድትጦሙ የተጻፈባችሁ ያ በእርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድ እና እውነትን ከውሸት ከሚለዩም ገላጮች አንቀጾች ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጡመው፡፡ شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የረመዷን ወር" ለሚለው የገባው ቃል “ሸህሩ ረመዷን” شَهْرُ رَمَضَان መሆኑን ልብ አድርግ! ይህ ወር የጸጋ ወር ስለሆነ በዒባዳህ ለሚዘወተሩ የጀነት ደጆች ክፍት የሆነበት፥ በተቃራኒው የእሳት ደጆች የሚዘጉበት ነው። እንዲሁ ማሪድ የሚባሉት ኩፋሩል ጂን የሚባሉት ሸያጢን የሚታሰሩበት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 30, ሐዲስ 9
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው የአላህም መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”የረመዷን ወር ሲጀመር የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፣ የጀሃነም ደጆች ይዘጋሉ፣ ሰይጣናትም ይታሰራሉ”። سَمِعَ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ إِذَا دَخَلَ شَهْرُ رَمَضَانَ فُتِّحَتْ أَبْوَابُ السَّمَاءِ، وَغُلِّقَتْ أَبْوَابُ جَهَنَّمَ، وَسُلْسِلَتِ الشَّيَاطِينُ ”
128 viewsኢስላም ከሚደፈር አጥንቴ ይሰበር رَّبِّ زِدْنِي عِلْمًا, 22:02