እህቴ የጎዳኝ ሰው በይቅርታው ያድነኛል ብለሽ አትጠብቂ!
ይልቅስ አንቺ ይቅር በማለትሽ ለሌላ ሰው ሳይሆን ለአንቺ ለራስሽ ከበቀል ደዌ ፈውስ ታገኛለሽ ።
የይቅርታው ንጉስ ኔልሰን ማንዴላ (Madiba) እንዲህ ይላሉ...."በቀል ማለት መርዙን እራስ ጠጥቶ ሌሎች እንዲሞቱ የመጠበቅ ሞኝነት ነው።"
ስለሆነም ይቅርታሽ በውስጥሽ ካለው የበቀል መርዝ ያሽርሻል።
ለዚህም ነው #ይቅርታ 'የአለም ውዱ ስጦታ ነው' የሚባለው!
ልብ አድርጊ ይህን ውድ ስጦታ የምትሰጪው ለጎዳሽ፣ ላሳመመሽ፣ ላስለቀሰሽ፣ ላወረደሽ...በጥቅሉ ለማይገባው ሰው ነው።
ለምን ቢባል ደግሞ በይቅርታው ስጦታ አንቺ ከህመምሽ ስለምትፈወሺ ነው !
እህቴ እዚህ ጋር አንድ ነገር እንዳትረሺ.....
በይቅርታሽ ከባለፈው ትምህርት ትወስጃለሽ እንጂ የጎዳሽን ሰው ወደ ህይወትሽ እንደገና እንዲመልስ ትፈቅጅለታለሽ ማለት ግን አይደለም።
እርምጃሽ በማስተዋል ይሁን!
#ጥበብ እና #ማስተዋል ለሰው ልጅ በሙሉ!
-ሣሙኤል ተክለየሱስ
(የህይወት ክህሎት አሰልጣኝ እና የቢዝነስ አማካሪ)
========================
ሙዳዬ ንዋይ - የቢዝነስ ልህቀት