Get Mystery Box with random crypto!

የደብረ ዘይት ደብረ መድኃኒት አንቀፀ መድኃኒት ሰንበት ትምህርት ቤት

የቴሌግራም ቻናል አርማ anketsemedanitsnbttimhirtbet — የደብረ ዘይት ደብረ መድኃኒት አንቀፀ መድኃኒት ሰንበት ትምህርት ቤት
የቴሌግራም ቻናል አርማ anketsemedanitsnbttimhirtbet — የደብረ ዘይት ደብረ መድኃኒት አንቀፀ መድኃኒት ሰንበት ትምህርት ቤት
የሰርጥ አድራሻ: @anketsemedanitsnbttimhirtbet
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 198
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የደብረ ዘይት ደብረ መድኃኒት አንቀፀ መድኃኒት ሰንበት ትምህርት ቤት ነዉ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ቀኖና ዶግማ የጠበቁ ማንኛዉም አሰተማሪ ጹሑፎች ይቀረቡበታል የየዕለቱ ስንክሳሮች ይተላለፉበታል ለመቀላቀል @Anketsemedanitsnbttimhirtbet ይጠቀሙ ሰለተቀላቀሉን በእግዚአብሔረ ሰም እናመሰግናለን።
ለበለጠ መረጃ ሀሳብ አሰታያየት ጥያቄ ካሎት
@Anketse_medanit የሚለዉን ይጠቀሙ

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-09 19:04:11 ✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ግንቦት ፪ ❖

❖ ግንቦት 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+"+ ቅዱስ ኢዮብ +"+

+የትዕግስት አባት ቅዱስ ኢዮብ በቅዱስ መጽሐፍ ላይ
እንደተመለከትነው ያልተፈተነበት ነገር የለም:: ሐረገ
ትውልዱም
ከአባታችን አብርሃም ይመዘዛል::

*አብርሃም ይስሐቅን
*ይስሐቅ ኤሳውን
*ኤሳው ራጉኤልን
*ራጉኤል ዛራን
*ዛራ ኢዮብን ይወልዳሉ::

+ቅዱስ ኢዮብ የነበረው እሥራኤል በግብፅ በባርነት ሳሉ
ነበር:: ኢዮብ ይሕ ቀረህ የማይሉት ባለጠጋ: ደግና
እግዚአብሔርን
አምላኪ ነበር:: የኢዮብ ደግነት የተመሰከረው በሰው
(በፍጡር) አንደበት አልነበረም:: በራሱ በፈጣሪ አንደበት
እንጂ::

+በዚህ የቀና ጠላት ዲያብሎስ ግን ኢዮብን ይፈትነው
ዘንድ ከአምላክ አስፈቀደ:: ጌታችን የጻድቁን የትዕግስት
መጠን
ሊገልጥ ወዷልና ሰይጣን ኢዮብን በሐብቱ መጣበት::
በአንድ ጀምበርም ድሃ ሆነ:: እርሱ ግን ፈጣሪውን ባረከ::

+ሰይጣን ቀጠለ:- የአብራኩን ክፋዮች (ልጆቹን)
አሳጣው:: ኢዮብ አሁንም አመሰገነ::

+በሦስተኛው ግን ሰውነቱን በቁስል መታው:: ቁስል ሲባል
በዘመኑ እንደምታዩት ዓይነት አልነበረም:: ከሰው ሕሊና
በላይ
የሆነ አሰጨናቂ ደዌ ነበር እንጂ:: ጻድቁ የአንድ ወጣት
እድሜ ያሕል በመከራው ጽናት እየተሰቃየ ገላውን በገል
ያከው
ነበር::ከአፉ ግን ተመስገን ማለትን አላቁዋረጠም::

+በመጨረሻም ሰይጣን በሚስቱ መጣበት::
"እግዚአብሔርን ተሳደብ" አለችው:: እርሱ ግን መለሰ:-
"እግዚአብሔር ሰጠ:
እግዚአብሔርም ነሣ: ስሙ የተባረከ ይሁን::"

+ከዚሕ ሁሉ ነገር በኋላ እግዚአብሔር ሰይጣንን ከጎዳናው
አስወገደው:: ጤናውን: ሐብቱን: ልጆቹን ለኢዮብ
መለሰለት::
ካለው እድሜ ላይ 140 ዓመት ጨመረለት:: ጻድቅና
የትዕግስት ሰው ቅዱስ ኢዮብ በ248 ዓመቱ በዚሕች ቀን
ዐረፈ::

=>እግዚአብሔር አምላክ ከጻድቁ ትዕግስትና በረከት
አይለየን::

❖ግንቦት 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ (የትእግስት አባት)
2.አባ ቴዎድሮስ ሊቀ ምኔት (የታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ ደቀ
መዝሙርና የአቡነ አረጋዊ ጉዋደኛ)
3."22" ሰማዕታት (የአባ ኤሲ ማሕበር)

❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
2፡ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
3፡ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
4፡ ቅዱስ አቤል ጻድቅ
5፡ አባ ጳውሊ ገዳማዊ
6፡ አባ ሕርያቆስ ዘብሕንሳ

++"+ ወንድሞች ሆይ! የመከራና የትዕግስት ምሳሌ
የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ::
እነሆ
በትዕግስት የጸኑትን ብጹዓን እንላቸዋለን:: ኢዮብ እንደ
ታገሠ ሰምታቹሃል:: ጌታም እንደፈጸመለት አይታቹሃል::
ጌታ እጅግ የሚምር: የሚራራም ነውና:: +"+ (ያዕ.
5:10)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/Anketsemedanitsnbttimhirtbet
87 views@Đäŵã, 16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 16:08:14
"ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም"
በማርያም ልደት ምክንያት ዛሬ ደስታሆነ!!!
107 viewsAbay Getaneh, 13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 19:49:22 1/09/14 ዓ.ም
ልደታ ለእግዝእትነ ማርያም

በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበ መልዕክታት ወንጌልና ምስባክ፡፡

ዲ/ን - ገላ1÷1-13
ን/ዲ - 1ጴጥ 1÷8-13
ን/ካ - ግብ፡ሐዋ 7÷44-51

የዕለቱ ምስባክ:- መዝ 86÷1
መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን
ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን።
እምኵሉ ተዓይኒሁ ለያዕቆብ፡፡

ትርጉም
መሠረቶቹ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው
ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ
እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል፡፡

ወንጌል :- ሉቃ 1÷39-57
ቅዳሴ :- ዘእግዝእትነ(ጎሥዐ)
63 views@Đäŵã, 16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 18:16:36
59 views@Đäŵã, 15:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 18:16:36 እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

+*" ልደታ ለማርያም ድንግል "*+

ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ:
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ::
" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) "

=>የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኩዋ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን::

+ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል::

+እመቤታችን ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. 1:9)

+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ቀን: በሊባኖስ ተራራ ከ2,022 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

"ሙሽራዬ ሆይ! ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" (መኃልይ. 4:8)

=>ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች ልጅ የላችሁም በሚል ይናቁ ነበር::

+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ::
እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::

+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::

+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::

+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::

+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::

+እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች::
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . .
ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም)

+"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ."
"ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. 1:9)

+እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሳ ግንቦት አንድ ቀን ተወልዳለች::

=>የእመቤታችን የዘር ሐረግ:-
*አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ=
*በእናቷ:-
-ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና::
*በአባቷ በኩል:-
-ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል::

+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም: በሊባኖስ ተራራ ከ2,026 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

=>የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::

=>ግንቦት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ልደታ)
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቴክታና በጥሪቃ
4.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ (የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር

=>+"+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው እናታችን ጽዮን ይላል::
በውስጧም ሰው ተወለደ::
እርሱም ራሱ ልዑል መሠረታት:: +"+ (መዝ. 86:1-6)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/Anketsemedanitsnbttimhirtbet
61 views@Đäŵã, 15:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 16:23:47
59 views@Đäŵã, 13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 16:23:46 ✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ሚያዝያ ፴ ❖

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

=>እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ
ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት::
እግዚአብሔር
ግን ደግ ነውና ይሔው ሚያዝያን አስፈጸመን::

+ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ:-
*ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል::
*ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል
(ሙተዋል)::

+እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪዋን ዘመን ደግሞ ለንስሃና
ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን::

+"+ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ +"+

+በዚሕች ዕለት ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነ: ወንጌላዊ:
ሐዋርያ: ሰማዕት: ዘአንበሳና ርዕሰ ሊቃነ ዻዻሳት የተባለ
ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ግብፅ ውስጥ ዐርፏል::

+ቅዱስ ማርቆስ እናቱ ማርያም: አባቱ አርስጥቦሎስ
ይባላሉ:: በልጅነቱ ኦሪትንና የዘመኑን ጥበብ ሥጋዊ
በሚገባ ተምሮ
ክርስቶስን ከቤተሰቦቹ ጋር ተከትሏል::

+የመጀመሪያ ስሙ ዮሐንስ ሲሆን ከ120ው ቤተሰብ
በእድሜ በጣም ትንሹ (20 ዓመት) እርሱ ነበር:: ለ3
ዓመታት ከጌታ
እግር ሥር ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን
ተቀብሎ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ ደክሟል::

+በተለይ የግብፅና የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን አባት ነው::
ክህነትን ያገኘን ከርሱ ነውና:: ቅዱስ ማርቆስ 16 ምዕራፍ
ያለውን ወንጌሉን ሲጽፍ ኪሩብ ገጸ አንበሳ በቀኙ: ሊቀ
ሐዋርያት በግራው ሆነው ይራዱት ነበር::

+ቅዱሱ ክቅዱስ ዻውሎስ: ከበርናባስና ዼጥሮስ ጋር
ተጉዟል:: ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላ ሰሜን አፍሪካ
አካባቢ በዚህ ቀን [በ60 ዓ/ም አካባቢ]
አረማውያን ገድለውታል::

=>ዳግመኛ በዚህ ቀን የቅዱስ ማርቆስን ወላጆችን
እናስባቸው ዘንድ ይገባል::

❖ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ) የጌታ ቅን አገልጋይ
የነበረ፡፡

❖ቅድስት ማርያም (እናቱ)
*ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ:
*ጌታችንን ያገለገለች:
*ቤቷን ለሐዋርያትና ለጌታ በስጦታ ያበረከተች ቅድስት
ናት::

+ቤቷም (ጽርሐ ጽዮን) የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን
ስትሆን ይህች ቤት መንፈስ ቅዱስ ወርዶባታል::
የእመቤታችን ግንዘትም
ተከናውኖባታል::

❖እግዚአብሔር ከሐዋርያዊው ቅዱስ ቤተሰብ በረከትን
ያድለን::

=>ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ)
3.ቅድስት ማርያም (እናቱ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2.አባ ሣሉሲ ክቡር
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት

=>+"+ . . . እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ
ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ
ማርያም ቤት መጣ:: ዼጥሮስም የደጁን መዝጊያ
ባንኩዋኩዋ ጊዜ ሮዴ የሚሏት አንዲት አገልጋይ ትሰማ
ዘንድ ቀረበች:: የዼጥሮስ ድምጽ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ
ከደስታዋ የተነሳ ደጁን አልከፈተችም:: ነገር ግን ወደ
ውስጥ ሮጣ ዼጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች::
+"+ (ሐዋ. 12:12-15)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
56 views@Đäŵã, 13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-06 19:19:54
54 views@Đäŵã, 16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-06 19:19:53 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

❖ ሚያዝያ ፳፱ ❖

✞✞ እንኩዋን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርሐዊ በዓለ ልደትና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ ✞✞

+"+ ተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን ቅዱስ አርስጦስ ሐዋርያ ወአባ አካክዮስ ጻድቅ +"+

=>ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዕለት ከምታስባቸው ቅዱሳን ሐዋርያው ቅዱስ አርስጦስና አባ አካክዮስ ቅድሚያውን ይይዛሉ::

+"+ አርስጦስ ሐዋርያ +"+

=>ቅዱስ አርስጦስ ከ72ቱ አርድእት አንዱ ሲሆን ከጌታችን እግር ለ3 ዓመታት ቁጭ ብሎ የተማረ: ፈጣሪው ከዋለበት ውሎ: ካደረበት አድሮ: የእጁን ተአምራት ያየ: የቃሉንም ትምሕርት ያደመጠ ሐዋርያ ነው::

+ከጌታችን ዕርገት በሁዋላም በጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ወጥቷል:: መጀመሪያ ከዋኖቹ ሐዋርያት ጋር በረዳትነት አገልግሏል:: ከቆይታ በሁዋላ ግን ሃገረ ስብከት ተሰጥቶት ብዙ ነፍሳትን ማርኩዋል:: አሕዛብንም ካለማመን ወደ ማመን አምጥቷል::

+በነዚህ ጊዜያት ጭንቅ ጭንቅ መከራዎች ደርሰውበታል:: ቅዱስ አርስጦስ ሐዋርያ በተሰጠው መክሊት አትርፎ ፈጣሪውንም ደስ አሰኝቶ በዚሕች ቀን አርፏል::

+"+ አባ አካክዮስ +"+

=>ዳግመኛ በዚህ ቀን አባ አካክዮስ አርፏል:: ቅዱሱ ከሕጻንነቱ ጀምሮ ንጽሕናን ያዘወተረ: በገዳማዊ የቅድስና ሕይወቱ የተመሠከረለት ነው:: ምሑርነቱንና ቅድስናውን የተመለከቱ ሰዎች በኢየሩሳሌም ላይ ዽዽስናን ሹመውታል::

+በመንበረ ዽዽስናውም ላይ እያለ ዕረፍት አልነበረውም:: ኢ-አማንያን ይገርፉት: ያስሩት: ያረሰቃዩትም ነበር:: ቤተ ክርስቲያን ስለ ተጋድሎው ጻድቅ: የዋሕና ንጹሕ ብላ ትጠራዋለች::

=>እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ ረድኤት: ጸጋና በረከት ይክፈለን::

=>ሚያዝያ 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አርስጦስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
2.አባ አካክዮስ ዘኢየሩሳሌም (ጻድቅና ንጹሕ)
3.አባ ገምሶ ሰማዕት

=>ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት
2.ቅድስት አርሴማ ድንግል
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
5.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
6.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)

=>+"+ ሰብዓውም በደስታ ተመልሰው ጌታ ሆይ! አጋንንት
ስንኩዋ በስምህ ተገዝተውልናል አሉት:: እንዲህም
አላቸው:- 'ሰይጣንን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ
አየሁ:: እነሆ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ በጠላትም
ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችሁአለሁ::
የሚጐዳችሁም ምንም የለም:: ነገር ግን መናፍስት ስለ
ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ:: ስማችሁ ግን
በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ:: +"+
(ሉቃ.10:17-20)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/Anketsemedanitsnbttimhirtbet
59 views@Đäŵã, 16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ