Get Mystery Box with random crypto!

ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ4 የዩኒቨርስቲው ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት ሰጠ። ባሕር | Amhara Media Corporation

ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ4 የዩኒቨርስቲው ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት ሰጠ።

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 04/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰኔ 03/2015 ዓ/ም ባደረገው ስብሰባ ለ4 የዩኒቨርስቲው ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት ሰጥቷል።

በዚሁም መሰረት ፦

1ኛ. ዶ/ር ጌታቸው ዓለማየሁ ዳሞት ከግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ በአግሮኖሚ የሙሉ ፕሮፌሰርነት

2ኛ. ዶ/ር ንጉስ ጋብዬ ሀብቱ ከባሕርዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በኬሚካል ኢንጅነሪንግ ሙሉ ፕሮፊሰርነት

3ኛ. ዶ/ር መላኩ ዋለ ፈረደ ከሳይንስ ኮሌጅ በኢንቶሞሎጂ ሙሉ ፕሮፌሰርነት

4ኛ. ዶ/ር ፀጋዬ ካሳ ጎጂ ከሳይንስ ኮሌጅ በሥነ-ህዋ ሳይንስ ሙሉ ፕሮፌሰርነት እድገት ማግኘታቸውን ዩኒቨርሲቲ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

አንጋፋው ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት 60ኛ ዓመት የብርኢዮቤልዩ በዓሉን በማክበር ላይ ይገኛል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
ዲስከቨር አማራ አሚኮ https://www.facebook.com/DiscoverAmharaAMECO
አሚኮ ስፖርት https://www.facebook.com/AMECOSport
አሚኮ እውነታ ማጣሪያ https://www.facebook.com/AMECOFactCheck