አፄዎቹ ድል ቀንቷቸዋል !
የሀያ ስምንተኛው ሳምንት የ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በ ባህር ዳር ስታዲየም መካሄዱን ሲቀጥል ፋሲል ከነማ ድል ቀንቷቸዋል ። ሀዋሳ ከተማን የገጠመው ፋሲል ከነማ በ ሙጂብ ቃሲም ግብ ጨዋታቸውን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አጠናቀዋል ።
በዘንድሮ የውድድር አመት ሙጂብ ቃሲም በ ቤት ኪንግ የ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ ሶስተኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል ። ፋሲል ከነማ ዛሬ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ከመሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ አንድ ማጥበብ ችለዋል ።
የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ፋሲል ከነማ በ ሀምሳ ስምንት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ። ሀዋሳ ከተማ በ አርባ ሁለት ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል ።
በቀጣይ ፋሲል ከነማ ከ ኢትዮጵያ ቡና እንዲሁም ሀዋሳ ከተማ ከ መከላከያ የሚገናኙ ይሆናል ።
@Alphasportet