2022-03-31 20:18:32
መጽሐፈ ምንኃር የመጻሕፍት ምንጭ
ዲ.ን የሺበላይ በላቸው
"ምንኃር" ከገነት መነሻቸውን ያደረጉ ዐራቱ አፍላጋተ ወንዞች መነሻ ቦታቸው ገነት ምንኃር ከተባለ ምንጭ ነው። ያ ቦታ ወንዞች ወደዐራት ቦታ ሳይከፋፈሉ አስቀድሞ አንድ ሆነው የሚፈልቁበት ቦታ ምንኃር ይባላል።
ዐራቱ አፍላጋት ማን ማን ናቸው ቢሉ:-
አንደኛው ኤፍራጥስ የሚባለው ወንዝ ዘይት ነው።
ሁለተኛው ኤፌሶን የሚባለው ወንዝ ሲሆን እሱም ወተት ነው።
ሦስተኛው ጤግሮስ የሚባለው ወንዝ ማር ነው።
ዐራተኛው ግዮን እርሱም አባይ ነው የኢትዮጵያ ደም ሥሯ ማለት ነው።
እነዚህ ዓለምን የሚያጠጡ ዐራቱ ወንዞች መነሻቸው አንድ ምንጭ ነው እርሱም ምንኃር ይባላል።
ይህም መጽሐፍ በባቢሎን ግንብ በሰው ልጆች ኃጢአት ምክንያት የሰው ልጆች ቋንቋ ከመደበላለቁ አስቀድሞ ለሰው ልጅ ሁሉ ከሰማይ የተሰጠጸጋ ግዕዝ ቋንቋን የሚያብራራ የሚያመሠጥር ቀመረ ፊደልን የሚያሳይ አቡሻክርን የጠነቀቀ የጠፋ ማንነታችንን ከሥሩ ከምጩ የተቆመ ምንጭ በመሆኑ መጽሐፈ ምንኃር ተብሏል።
አንድም ከገነት ምንጭ ጥርት ያለ ምንም የሌለበት ንጹሕ ውኃ ይፍልቃል። እመቤታችንም “ነቅዓ ፈልፈለ ማየ ሕይወት - የሕይወት ውኃ ምንጭ” ናት(ውዳሴ ማርያም)፤ አማናዊ የሕይወት ውኃ ጌታችንን አስገኝታልናለችና።
በገነት ዐራቱ አፍላጋት ይወጣሉ፣ ገነትን ያጠጡና ወደዐራቱ አቅጣጫ ይፈሳሉ። እመቤታችንም “ፈልፈለ ማየ ሕይወት ዘይውሕዝ እምከርሱ - የሕይወት ውኃ ከሆዱ ይፈልቃል” ተብሎ የተነገረለት አማኑኤልን አስገኘች። ስለዚህ ይህም መጽሐፍ ማንነታችንን የምናገኝበት ከፍታችንን የምንወጥንበት ወደምንጫችን የምንመለስበት ኢትዮጵያዊነት ልዕልናችንን የምናገኝበት የዕውቀት ትንሣኤ የያዘ አብሣሬ ርግብ የሆነ መጽሐፍ ነው።
እውነትም መጽሐፈ ምንኃር ይነብብ ይነብብ ይነብብ ይነብብ እላለሁ።
186 viewsedited 17:18