Get Mystery Box with random crypto!

የአፍሪካ ሀገራት በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ሰላም እንዲወርድ ለማስቻል የልኡካን ቡድን ለአደራዳ | AHADU RADIO FM 94.3

የአፍሪካ ሀገራት በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ሰላም እንዲወርድ ለማስቻል የልኡካን ቡድን ለአደራዳሪነት ሊልኩ መሆናቸው ተገለጸ፡፡

ስድስት የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችን የሚያካትት የልኡካን ቡድን በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል ያለውን ወጥረት በማርገብ ሰለም እንዲወርድ ለማስቻል እየተንቅሳቀሱ እንደሚገኙ የደቡብ አፍረካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማ ፎሳ አስታውቀዋል፡፡
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎደሜር ዘለንስኪ የልኡካን ቡድኖቹን በየመዲናዎቻቸው ለመቀበል መስማማታቸውም ተገልጿል፡፡
የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ከሁለቱም ሀገራት ፕሬዝዳንቶች ጋር ባሳለፍነው የእረፍት ቀናት ውስጥ ረጅም የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን አያይዘው ይፋአድርገዋል፡፡

ሲሪል ራማ ፎሳ ይህ ለሰላም የማደራደር እና የማስማማት ጽንሰ ሀሳብ ከዛምቢያ፣ ሴኔጋል፣ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ፣ ዩጋንዳ፣ ግብጽ እና ደቡብ አፍሪካ የመጣ እንደሆነም አብራርተዋል፡፡
በዚህ የሰላም ድርድር ሂደት ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ረዘም ያለ ውይይት እንደሚደረግ እና የሁለቱም ሀገራት መሪዎች ጥያቄውን በመልካም መቀበላቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ዘገበው፡- የኔሽን ኒውስ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24