Get Mystery Box with random crypto!

ቡርኪራፋሶ በጂሃድ ሀይሎች ላይ የተጀመረውን ጥቃት ለማጠናከር ስዓት እላፊ ገደብ መጣሏ ተነግሯል፡፡ | AHADU RADIO FM 94.3

ቡርኪራፋሶ በጂሃድ ሀይሎች ላይ የተጀመረውን ጥቃት ለማጠናከር ስዓት እላፊ ገደብ መጣሏ ተነግሯል፡፡

ቡርኪናፋሶ በስተ ሰሜንና በማእከላዊ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል የጀመረችውን የጂሃዲስቶች ጥቃት አጠናክራ ለመቀጠል በሚል የስዓት እላፊ ገደብ መጣሏን አስታውቃለች፡፡

በሳህል ቀጣና ያለችዋን በድህነት የምትጠቀሰዋ ሀገር ቡርኪናፋሶ ለረዥም ጊዜ በተካሄደባት የጂሃድ ሀይሎችና የአሸባሪዎች ጥቃት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ንጹሃንን የፖሊስና የጦር ሀይል አባላት ህይወታቸውን እንዳጡ ሲገለፅ ከሁለት ሚሊየን በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸውና ከቀያቸው መፈናቀላቸው ይታወቃል፡፡

ከትናንት ምሽት ጀምሮ በቡርኪናፋሶ የተጣለው የስዓት እላፊ ገደብ የሰዎችን እንቅስቃሴ እንዲሁም የሁለት እግርና የአራት እግር ተሸከርካሪዎችም እንዳይንቀሳቀሱ የሚከለክል ነው፡፡

በቡርኪናፋሶ ከማሊ አዋሳኝ በምትገኘዋ ኮል ፔሎጎ ግዛት የተጣለው የስዓት እላፊ ገደብ የተያዘው የመጋቢት ወር እስኪጠናቀቅ ድረስ እንደሚቆይ የዘገበው ኔሽን ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24