2022-07-19 20:18:30
በክልሉ ካሉ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ከተውጣጡ መሃንዲሶች ጋር ውይይት ተካሄደ ፡፡
=============
የአፋር ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፅ/ቤት በስሩ ከሚገኙ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ከተውጣጡ መሃንዲሶች በትራንስፈርመር ደህንነት ዙሪያ ዛሬ በፅ/ቤቱ ውይይጥ ተደርጓል ፡፡
በውይይቱ ላይ የተገኙት የክልል ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ያሲን አሊ እንዳብራሩት ትራንስፈርመሮች ለተቋሙ ፋብሪካዎቻችን በመሆናቸው ደህንነታቸውን መጠበቅ የመሃንዲሶች ዋና ስራ በመሆኑ ሁሉም በየማእከላቱ በሃላፊነት በመስራት በ2015 በጀት አመት የትራንስፈርመሮች ደህንነት ተጠብቆ መሰራት እንዳለበትና የትራንስፈርመሮችን መቃጠል ለመቀነስ በትጋት መሰራት እንዳለባቸው አብራርተዋል ፡፡
በውይይቱም ወቅት በተለይም ከሃይል መቆራረጥና መሰል ችግሮች ዙሪያ ሙያዊ እገዛ በመስጠት ለቅድመ ጥገና ስራ ግብአት የሚሆኑ መረጃዎችም በመሰብሰብና በመቀመር ማዘጋጀት እንዳለባቸው የተቆሙ ሲሆን በተለይም ከፌር ፕሮጀክ የሚገኙ ግብአቶችን እና መረጃዎችን በመጠቀም በትራንስፈርመር፣ በመካከለኛ እና ዝቅተኛ መስመሮች ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል ፡፡
የአፋር ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/100068806796522/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ https://t.me/afeeu
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et/
640 viewsbirhanu adane, 17:18