ታሪካዊው የድሬዳዋ አሸዋ ሜዳ በቆሻሻ መሞላት በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ ፈጠረ በድሬዳዋ ከተማ የሚገኘው ታሪካዊው የአሸዋ ሜዳ ታሪኩን በማይመጥን ቆሻሻ መሞላቱ ነዋሪዎች ላይ ቅሬታ ፈጥሯል። የከተማው ፅዳትና ውበት ኤጀንሲ ሜዳው አሁን ላይ በቀላሉ ማፅደት ወደማይቻልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጿል። ኢንስትራክተር መሰረት ማኔ በአፍሪካ ግዙፍ መደበኛ ውድድሮች ወይም በፕሪምየር ሊግ ውድድር ላይ የመጀመሪያዋ ሴት አሰልጣኝ ናት። ኢንስትራክተር መሠረት እስካሁን በስፖርቱ ዓለም ያገኛቻቸው ስኬቶች መነሻ ይኸው ታሪካዊ የአሸዋ ሜዳ መሆኑን ትናገራለች። ላገኘችው ዝናና ክብር ያበቃት አሸዋ ሜዳ አሁን ላይ በቆሻሻ ተሞልቶ መመልከቷ እንደሚያሰቆጫት ለአዲስ ዘይቤ የተናገረችው ኢንስትራክተር መሠረት ማኔ፣ የሚመለከተው አካል ቁጥጥር ማነስ እና የህብረተሰቡ የግንዛቤ እጥረት ለሜዳው ታሪክ መጠለሸት ምክንያት እንደሚሆኑ አስቀምጣለች። https://am.addiszeybe.com/featured/dire-dawa/%E1%8C%A4%E1%8A%93/history/current-affairs-am/the-filling-of-the-historical-dredawa-sand-field-with-garbage-caused-complaints-among-the-residents 533 views09:31