በአማራ ክልል ሁለት የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅት ሰራተኞች ሲገደሉ ሌሎች ሁለት መቁሰላቸው ታወቀ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል የሰሜን ጎንደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አምቡላንስ ሾፌርና አዋላጅ ነርስ የሆኑ ሠራተኞች ላይ “ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂ ኃይሎች” ጥቃት ፈፅመዋል ብሏል። የዩናይትድ ስቴትስ የካቶሊክ ዓለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅት የሆነው ካቶሊክ ሪሊፍ ሰርቪስስም በተመሳሳይ ሁለት ሠራተኞቹ በታጣቂዎች መገደላቸውን አስታውቋል። እሁድ ሚያዝያ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ቹኦል ቶንጊክ የተባለው የደህንነት ስራ አስኪያጅ እንዲሁም አማረ ክንደያ የተባለው የአሜሪካ ካቶሊክ እርዳታ ድርጅት ሹፌር በአማራ ክልል በድርጅቱ ተሽከርካሪ ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ ተገድለዋል ሲል ድርጅቱ በድረ ገፁ አስታውቋል። ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/addis-ababa/%E1%8B%9C%E1%8A%93/politics-am/current-affairs-am/in-the-amhara-region-two-humanitarian-aid-workers-were-killed-and-two-others-were-injured 885 views13:41