በቴዲ አፍሮ የህይወት ጉዞ ላይ የሚያውጠነጥን አዲስ መጽሐፍ ለገበያ ሊበቃ ነው
በክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ የህይወት ጉዞ ላይ የሚያውጠነጥን "ቴዎድሮስ እስኪነግሥ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ከሀምሌ 20/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።
መጽሐፉ በዘላለም ሙሉ የተፃፈ ሲሆን የፊታችን ረቡዕ ለገበያ እንደሚቀርብ ነው የተነገረው።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ #ልክ_በዛሬዋ_እለት ዝግጅታችን የብላቴናው ልደት ዛሬ መሆኑን እናንሳ። ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ልክ በዛሬዋ እለት ሐምሌ 7 1968 አ.ም ነበር በአዲስ አበባ የተወለደው።
ዛሬ 46ተኛ የልደት በአሉን እያከበረ ሲሆን አድናቂዎቹም በያመቱ ለሱ ያላቸውን ክብርና ፍቅር ለመግለጽ ቀኑን ደም በመለገስና በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ያከብሩታል።
@Addis_News
@Addis_News