"የህዝብ አመኔታን መቼም ቢሆን አንዘነጋም፤ ክብራችን ህዝብን በፍትሃዊነት ማገልገል ስለሆነ" :- ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ሌቦችና እምነታቸውን ሸጠው የሚበሉ ሁሉ ለጊዜው ቢታግሉንም አያሸንፉንም፤ እውነት ምንግዜም ታሸንፋለች!! ከሁሉም በላይ ፈጣሪ ረድቶን የህዝብን ሀብት በቴክኖሎጂ ዉንብድና ከመዘረፍ ማዳን ችለናል ። የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ስራ ላይ አጠራጣሪ ጉዳዮች ከገጠሙ ጊዜ አንስቶ በማጣራት ሂደት ለደገፋችሁን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የኢኖቨሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርንና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትን ከልብ ላመሰግን እወዳለሁ። @Addis_News @Addis_News 7.9K viewsedited 05:00